spot_img
Sunday, September 24, 2023
Homeዜናአገልግሎት ያቋረጡ 18 ሚሊየን ሲም ካርዶች በአዲስ መልክ ለገበያ ሊቀርቡ ነው

አገልግሎት ያቋረጡ 18 ሚሊየን ሲም ካርዶች በአዲስ መልክ ለገበያ ሊቀርቡ ነው

advertisement

ቦርከና
ኅዳር 24, 2011 ዓ.ም.

የመቀበልም ሆነ የመደወል አገልግሎት ያቋረጡ 18 ሚሊየን ሲም ካርዶች በአዲስ መልክ ለገበያ ሊቀርቡ መሆኑን ኢትዮ ቴሌኮም አስታዉቋል።አሁን ላይ ኩባንያው ያስቀመጣቸውን ደረጃዎች በሙሉ ጨርሰው አገልግሎት መስጠት ያቆሙ የሞባይል ቁጥሮች 18 ሚሊየን ደርሰዋል።

አርትስ እንደዘገበው ኩባንያው እነዚህን ቁጥሮች ለገበያ የሚያውላቸው ደንበኞቼ የተሰጣቸውን ጊዜ ገደብ ባለመጠቀማቸውና አገልግሎት መጠቀም ካቆሙ ከረጅም ጊዜ በላይ የቆዩ በመሆናቸው ነው ብሏል።

አንድ የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኛ አዲስ የሞባይል ሲም ካርድ ቁጥር ካወጣ በኋላ ተደጋጋሚ አየር ሰዓት የሚሞላ ከሆነ ሳይሞላ መስመሩ ሳይዘጋ ለ120 ቀናት ይቆይ የነበረ ሲሆን፥ በ120 ቀናት ውስጥ ከሞላም አገልግሎት እንደሚቀጥል ይታወቃል።

ከ120 ቀናት በኋላ ግን የሞባይል አገልግሎቱ መደወል ሳይችል ከሌላ ወገን ጥሪዎችንና መልዕክቶችን እያስተናገደ ለ330 ቀናት ይቆይ እንደነበረም ነው የተገለጸው።በእነዚህ ቀናት ውስጥ የአየር ሰዓት የማይሞላ ከሆነ ግን መስመሩ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት የሚያቋርጥ ይሆናል። እነዚህ የሞባይል ቁጥሮች ሀብት ስለሆኑ ለአዳዲስ ደንበኞች በአዲስ መለያ ለመስጠት ዳግም ገበያ ላይ በቅርቡ ለገበያ ይውላል ።

ከአሁን በፊት አንድ ደንበኛ አዲስ የሞባይል ቁጥር አውጥቶ አየር ሰዓት መሙላት ካቆመና መስመሩ መወደልም ሆነ መቀበል ካቆመበት ቀን ጀምሮ፥ በሶስት ዓመት ውስጥ ያን ቁጥር ወደ ኩባንያው ቅርንጫፎች በመጓዝ ዳግም ማውጣት ይቻል ነበር።ይህ የቆይታ ጊዜ በአሁኑ ሰዓት ወደ አንድ አመት ዝቅ ማለቱን ኩባንያው ገልጻል ።

ኢትዮ ቴሌኮም አሁን ላይ ያሉት ደንበኞች የሚጠቀሙት አብዛኛዎቹ የድምፅ አገልግሎት ቢሆንም፥ የኢንተርኔት አገልግሎትን አሁን ካለበት ደረጃ ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር የተለያዩ እቅዶችን ነድፎ እየተንቀሳቀሰ መሆኑም ታውቋል።

በፍሬህይወት ዮሃንስ
_____
ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,682FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here