- Advertisement -
ቦርከና
ኅዳር 25, 2011 ዓ.ም.
የአፋር ብሄራዊ ዴሞክራሲዊ ፓርቲ /አብዴፓ እያካሔደ ባለው ሰባተኛ መደበኛ ጉባኤው ሰባት የፓርቲው አባላትን የአዘጋጅ ኮሚቴውን ሪፖርት ካዳመጠ በኋላ የፕሬዝዲየም አባል አድርጎ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል።
በዚህም መሰረት
1ኛ- አምባሳደር ሃሰን አብዱልቃደር
2ኛ- አወል አርባ
3ኛ-ኢንጂነር አይሻ መሃመድ
4ኛ- አሊ ሁሴን
5ኛ- አባሂና ኮባ
6ኛ-ዛህራ ሁመድ
7ኛ-አህመድ ሱልጣን
የፕሬዚዲየም አባላት ሆነው የተመረጡ ሲሆን አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃደርን ሰብሳቢ ኢንጂነር አይሻ መሃመድን ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ መምረጡን ኢዜአ ዘግቧል።በቀጣይም ጉባኤውን የአዘጋጅ ኮሚቴን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አድምጦ አፅድቋል፡፡
በፍሬህይወት ዮሃንስ
__
ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።