በመስከረም አበራ
ለቪዥን ኢትዮጵያ የቀረበ ታህሣስ 18-19 , 2011 ዓ.ም.
የጥናቱ ጨመቅ(Abstract)
ሃገራችን አሁን የምትገኝበት ሁኔታ ዲሞክራሲያዊ ሽግግርን የሚከለክል ስላልሆነ የሽግግር መንግስት ማቋቋም ሳያስፈልግ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት የሚያስችል የሽግግር ስራ መስራት ይቻላል፡፡ ይህን ሽግግር ለማድረግ ሃገሪቱ ለረዥም ዘመን ዲሞክራሲን እንዳታሰፍን ያደረጉ ችግሮችን በሽግግሩ ወቅት አቃሎ በምርጫ ለሚመጣው መንግስት ለዲሞክራሲያዊ አስተዳደር የሚመች ሁኔታ መፍጠር ያስፈልጋል፡፡ የዚህ ፅሁፍ አላማ እነዚህን ችግሮች ለይቶ የሚፈቱበትን መንገድ መጠቆም ነው፡፡ ይህን ለማድረግ የተለያዩ መፅሃፍት፣ጥናታዊ ፅሁፎች እና ተመሳሳይ ለውጥ ያደረጉ የአለም ሃገራት ልምድ ዳሰሳ ተደርጓል፡፡ በተጨማሪም የፅሁፉ አቅራቢ እይታዎች ግብዓት ተደርገዋል፡፡ ከተዳሰሱ መዛግብት በተገኙ መረጃዎች መሰረት ሃገራችን ዲሞክራሲን እንዳታሳድግ ካደረጉ ችግሮች ውስጥ ህገ-መንግስታዊ መሰረት ያላቸው እንደ የዘውግ ፖለቲካ/ፌደራሊዝም፣የመሬት ባለቤትነት ጉዳይ፣ፓርላመንታዊ የመንግስ ስርዓት እና ኢህአዴግ የመሰረተው የፓርቲ ፖለቲካ ዘይቤ ዋነኞቹ ናቸው፡፡እነዚህ ችግሮች በታሪክ እየተጠራቀሙ የመጡ በመሆናቸው በሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች በተሳተፉበት ሰፊ ስራ እና በህዝብ ውይይት በሽግግሩ ወቅት መፈታት አለባቸው፡፡ ችግሮቹ በሽግግሩ ወቅት ሳይፈቱ በምርጫ ወደ ሚመረጠው መንግት ከተላለፉ የሚመረጠውን መንግስትም ሆነ የሃገሪቱን ህልውና አደጋላይ ሊጥሉ ይችላሉ፡፡በተቃራኒው ታሪካዊ ችግሯን የፈታች(ያቃለለች) ሃገር ለተመራጩ መንግስት ማስተላለፍ ከተቻለ ተመራጩ መንግስት ታሪካዊ ችግሮችን የመፍታት አስቸጋሪ ስራ ውስጥ ሳይገባ ሃገሪቱን ወደ ዲሞክራሲያዊ መስመር የሚያስገቡ ስራዎችን ወደ መስራቱ እንዲገባ ይረዳዋል፡፡ይህን ገቢራዊ ለማድረግ ታሪካዊ ችግሮችን መርምሮ፣የእልባት መንገድ አፈላልጎ፣ሽግግሩን/ለውጡን የሚያፀኑ ስራዎችን በመስራት ሃገር የሚያሻግር፣ ይህን ለማድረግ በቂ ስልጣን የተሰጠው ተቋም መዋቀር አለበት፡፡
ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
___
ማስታወሻ:በዚህ ጽሁፍ ላይ የተንጸባረቁ ሳሃቦች የጸሃፊውን/የጸሃፊዋን እንጂ የድረገጹን አቋም አያንጸባርቁም። ነጻ አስተያየት ወይንም ሃሳብ በዚህ ድረ ገጽ ለማውጣት ጽሁፍዎትን በ info@borkena.com ይላኩልን።