spot_img
Wednesday, March 22, 2023
Homeአበይት ዜናበወለጋ ጊምቢ ዞን ዲላ ጎላላ ጉሊሶ ወረዳ በአማራ ተወላጆች ላይ በደረሰ ጥቃት...

በወለጋ ጊምቢ ዞን ዲላ ጎላላ ጉሊሶ ወረዳ በአማራ ተወላጆች ላይ በደረሰ ጥቃት ቢያንስ 200 ሰዎች አለቁ

- Advertisement -
አማራ እልቂት

ቦርከና 
ጥቅምት 23፣ 2013 ዓ ም 

በወለጋ ጊምቢ ዞን ዲላ ጎላላ ወረዳ እሁድ አመሻሽ ላይ የአማራ ተወላጆች ላይ በተደረገ ጭካኔ የተሞላበት ጥቃት ቢያንስ 200 ሰዎች እንዳለቁ ተሰማ ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎችን ዋቢ ያደረጉ ዘገባዎች አሳውቀዋል፡፡

በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤቶችም እንደተቃጠሉ ተሰምቷል፡፡ 

ይህ እጂግ ዘገኛኝ ነው የተባለ እልቂት የኦነግ ሽኔ ታጣቂዎች እንዳደረሱ የክልሉ መንግስት አስታውቋል ሆኖም የሟቾችን ቁጥር አላሳወቀም፡፡ የህወሓትንም ቡድን አብሮ ኮንኗል፡፡ 

በወረዳው የሚኖሩ አማራዎች ለውይይት በሚል ለስብሰባ ከተጠሩ በኋላ ተከብው በተኩስ ሩምታ እንደተገደሉም ነው የተሰማው፡፡

ድርጊቱ የተፈጸመው በአካባቢው ተሰማርቶ የነበረው የመከላከያ ኃይል እንዲወጣ ከተደረገ ከአንድ ቀን በኋላ ነው፡፡ ሰራዊቱ እንዲወጣ ያዘዘው የመንግስት አካል እና ለምን ሰራዊቱ እንዲወጣ እንደታዘዘ የታወቀ ነገር የለም፡፡ 

በአማራ ላይ ያነጣነረ እልቂት በተለያዮ የኢትዮጵያ ክፍሎች በተደጋጋሚ እንደተፈጸመ የሚታወስ ሲሆን ሁኔታው እየተባባሰ በመሄድ ላይ መሆኑን ባላፉት ሁለት ወራቶች የደረሱት እልቂቶች ያመላክታሉ፡፡ 

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,440FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

1 COMMENT

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here