- Advertisement -

ህዳር 2 2013 ዓ ም
በመጨረሻም የወልቃይት ጠገዴ ጠለምት ህዝብ በወገኖቹ የዐማራ ታጋዮችና የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጀግንንት ትግል ከትህነግ ወያኔ አገዛዝ ነፃ ወጣ!
እንደሚታወቀው በ1972 ዓ.ም ትህነግ ወያኔ የተከዜን ወንዝ ተሻግራ ለሙን የወልቃይት እና የአካባቢውን መሬት በወረራ ከያዘችበት ጊዜ አንስቶ የወልቃይት ጠገዴ ጠለምት ዐማራ ህዝብ በነዚህ ወራሪ እና ተስፋፊ ቡድን የዘር ማጥፋት፣ ማፈናቀል የርስት ወረራ የማንነት ቅየራ እና በሰው ልጅ ላይ ሊደርስ የማይገባ አሰቃቂ ግፍ ተፈጽሞበታል። ላለፉት አርባ አምስት ዓመታትም ለደረሰበት የዘር እልቂት ፍትህን ለማግኘት የተነጠቀውን ርስት እና ማንነቱን ለማስመለስ ከትህነግ ወንበዴ ጋር ሲተናነቅ ቆይⶆል። ይህ ለአራት አስርት ዓመታት የተደረገው ትግል ጊዜው ሲደርስ በጀግኖቹ የአማራ ታጋዮች ተጋድሎ ወልቃይት እና አካባቢው ከወራሪው ትህነግ ወያኔ አገዛዝ ነፃ ሆኗል፡፡