spot_img
Saturday, September 30, 2023
Homeነፃ አስተያየትበአፉር በአማራና በኤርትራ ሕዝብ ላይ የተደቀነው አደጋ!!

በአፉር በአማራና በኤርትራ ሕዝብ ላይ የተደቀነው አደጋ!!

advertisement

 ከቴዎድሮስ ሃይሌ 

 ሕወሃት የኢትዮጵያ ሕልውና ለማፍረስ የሰሜን ዕዝን አጥቅቶ የለኮሰውን የክህደት ጦርነት በአጭሩ እንዲቀጭ የኤርትራ መንግስት ሚና ቀላል አልነበረም:: የከሃዲው ቡድን ጎምቱ መሪዎች እንዲደመሰሱ ሕወሃትም ክንፉ ተሰብሮ ወደ ተንቤን ሸለቆ እንዲያፈገፍግ የኤርትራ እገዛ ወሳኝ ነበር:: ይህ የኤርትራ ሰራዊት ወገናዊ ድጋፍ ምንም ለጋራ ደህንነት ቢሆንም ኢትዮጵያውያን የማይዘነጉት የታሪክ አጋጣሚ ነው::  

ለዘለቄታውም ሻክሮ ለኖረው ለሁለቱ ሃገር ሕዝቦች በመተሳሰብ ላይ የተመሰረተ አብሮነት እንዲጠናክር የሚረዳም አጋጣሚ ነው::  

 የኢትዮጵያና የኤርትራ ሕዝብ ባለፉት ዘመናት ለብዙ መከራና መለያየት ቢዳረግም ሊበጠስ በማይችል የረጅም ዘመን የአብሮነት ታሪክ የተሳሰረ ነው:: በተለይም ኤርትራን በቀጥታ ድንብር የሚጋሩት  የአማራና የአፉር ኢትዮጵያውያን ከጉርብትናውም በላይ በበዙ ማህበራዊና ባህላዊ መስተጋብሮች የተቆራኙ ናቸው:: የአንዱ ልማትም ሆነ ጥፉት ለሌላኛው ያለው ተጽዕኖ እጅግ በጣም ቅርብ ነው::  

 የአማራ የአፉርና የኤርትራ ሕዝብ ሰላምና ደህንነቱ ተረጋግጦ ወደ ልማትና ብልጽግና የሚያደርገውን ጉዞ ሊያደናቅፍ የተነሳውን ቅጥረኛውን የሕወሃት ጁንታ በጋራ ተፉልሟል:: ሕወሃት ለነዚህ ሕዝቦች የህልውናጠላት መሆኑን በተጨባጭ ያረጋገጠና ወደፊትም ከተሳካለት በነዚህ ሕዝቦች ላይ ሊፈጽም የሚችለው ሰቆቃየከፉ እንደሚሆን ማስረጃ ማጣቀስ አያስፈልገውም:: ለዚህም ነው ሕወሃትን አምርረው በመታገል ላይ ያሉት:: 

 ከዚህም በላይ የሕወሃት ሕልውናን በማያዳግም መንገድ መቋጨት ለኢትዮጵያውያ ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ አፍሪካ ጭምር እፎይታ ነው:: ሕወሃት የሽብር ሃይል የውጪ ሃይሎች ተላላኪ ጸረ ሕዝብ በመሆኑ በማንኛውም መንገድ ከድምሰሳ ተርፎ የቀጠናው ስጋት እንዲሆን የሚተባበረውን ጭምር መዋጋት አማራጭ የሌለው ግዴታ ነው:: የኤርትራ ሕዝብ ሰላምና ብልጽግና የአማራና አፉሩ ማህበራዊ እረፍትና ልማት የሚረጋገጠው የሕወሃት እስትንፉስ ሲዘጋ ብቻ ነው:: 

 የኤርትራን ሕዝብ ለማንበርከክ በሕወሃት ደላላነትና በጌቶቹ የምዕራቡ ዓለም ደም መጣጭ ኒዖ ኮሎኒስታዊ ሃይሎች ቀጥተኛ ውሳኔ ላለፉት 20 አመታት በመራር የኢኮኖሚ ማዕቀብ ተንገላቷል:: አማራ እንደ ሕዝብ ቃላት ሊገልጹት ከሚችሉት በላይ የሕወሃት የበቀል ሂሳብ ተወራርዶበታል:: አፉር ኢትዮጵያዊነት ማስቀደሙ ከባድ ዋጋ አስከፍሎታል:: ሌሎች ኢትዮጵያውያንም የሕወሃት የግፍ ሰለባ መሆናቸው ባይዘነጋም በነዚህ ሦስት ሃይሎች ላይ ከደረሰው ጋር ግን አይስተካከልም::  

 ሕወሃት ተራ የመንደር ሽፍታ ተደርጎ ሊናቅ የማይችል በቀጠናው ጂዖ ፖለቲካዊ ፍላጎት ያላቸው የተለያዩ ሃይሎች ለሽብር አላማ ሊጠቀሙበት የሚፈልጉት ሃይል ነው:: የወንበዴው ቡድን መሪዎች እንኳን ለሌላው በስሙ ለሚነግዱበትን ለትግራይ ሕዝብ ጭምር ግድ የላቸውም:: ከግል የበቀልና የስልጣን ጥማቸው እና ከቁስ ሰቀቀናቸው ባሻገር ምንም የማይታያቸው ጭራቆች በመሆናቸው በተባበረ ክንድ ከስራቸው ተነቅለው እስካልተወገዱ ድረስ ቀጠናው ወደ ሰላምና ልማት ፈጽሞም አይሸጋገርም::

 ሕወሃት አንብሮት በኖረው እርኩስ የፖለቲካ ርዕዮት አጠቃላዩ የኢትዮጵያ ሁኔታም በብዙ ችግሮች የተተበተበ እንደሆነ ቀጥሏል:; ሃገሪቷ ካለችበት የቀውስ እዙሪት ለመውጣት የምትችልበት መሪ እቅድና ፕላን መንግስት እጅ ስለመኖሩ አይታወቅም:: የመንግስት ፖሊሲና የአፈጻጸም ብቃትና ቁርጠኝነት ከሁኔታው በታች ነው::ሕወሃት ከፉፍሎ ለመግዛት እንዲመቸው በኢትዮጵያ ላይ ደንግጎት የኖረው ሕገ መንግስትም ዛሬም ከተተከለበት የዘር ማጥ አልተነቀለም::  

 ይህው የአራዊት ሕግ ኢትዮጵያን ፈንጂ ላይ የቆመች ሃገር አድርጏታል:: በዘር ፖለቲካ ቋያ የምትንገበገብ በውስጥ አድሃሪ በውጪ የቅጥረኛ ማዕበል የምትናጥ አደጋ የተቆራኛት ሃገር ሆናለች:: የዚህ ሁሉ ጥፉት አጋፉሪው ሕወሃት በመሆኑ በዚህ ቡድንና ይዞት በኖረው ጨለምተኛ ተረኮቹ ላይ የሚወሰድ አቋም የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካ ቀንድን ሁኔታ ይወስናል:: 

 ፕሬዜደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ባለፈው ሳምንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የኢትዮጵያን ሁኔታ ዝም ብለው እንደማይመለከቱ ተናግረዋል:: በተለይም በኢትዮጵያ የተንሰራፉው የዘር ፖለቲካ በጣም እንደሚያሳስባቸው ገልጸዋል:: ኢትዮጵያ ከዘር ፖለቲካ ተላቃ በዜግነት ላይ የተመሰረተ ስርዐት እንድትመራ ያላቸውን ቀና ምኞት በይፉ አሳውቀዋል:: 

 ይሄ የኤርትራው መሪ አቋምና እምነት በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚያምኑበትና ብዙ ዋጋም የከፈሉበት ወሳኝ ጉዳይ ነው:: እንደ ሃገር የመዳኛም መንገድ ነው:: በአንጻሩም ሕወሃትና ተንበርካኪ ግልገሉ ኦነግ በዘር ፖለቲካ የቆረቡና እስከ ምጽዐት እንዲቀጥል የሚፈልጉ ናቸው:: ይህንንም ሕልማቸውን ለማሳካት በቅንጅት ኢትዮጵያን ለማፍረስ ኦነግና ሕወሃት ቃልኪዳናቸውን አድሰው በጋራ ብዙ ውድምት ማድረሳቸን አይተናል::  

 ሕወሃትና አስተሳሰቡ ከኢትዮጲያ የፖለቲካ ሜዳ ውስጥ ሊመለስ እንዳይችል መቀበር እንዳለበት አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ያምናል:: ለተግባራዊነቱም ተንቀሳቅሷል:: ነገርግን ከቅርብ ግዜ ወዲህ ሕወሃትን በተመለከተ የኢትዮጵያ መዐከላዊ መንግስትና ጠቅላይ ሚንስትሩ የሚያራምዱት አቋም ግልጽነቱ በጣም አጠያያቂ እየሆነ መጥቷል:: ሽብርተኛው የሕወሃት ሃይል ላይ የሚወሰድ ማንኛውም ውሳኔ የአማራና የአፉርን ጥቅም እንዲሁም የኤርትራን ደህንነት ታሳቢ ያደረገ አካሄድ ለሁሉም የሚበጅ መሆኑ አያጠራጥርም:: 

 ለቀንደኞቹ ወንጀለኛ የሕወሃት መሪዎች የተሰጠው ምህረት እና እነ ጌታቸው እረዳ የሰላም ጥረቱን የኤርትራ መንግስት እያደናቀፈ ነው ብለው መክሰሳቸው ; የጠቅላይ ሚንስትር አብይ መንግስት በስውር ከሕወሃት ጋር እየተደራደረ ነው የሚል ግምት ብዙሃኑ እንዲያምን እያደረገው መጥቷል:: 

 ይህንና የመንግስትን ግልጽነት የጎደለው ውሳኔ ሴራ ተንታኞችና የፖለቲካ ተቃዋሚዎች የሚያነሱት አጀንዳ ተዐማኒ እንዲሆን አስችሎታል:: በርካታ ግራ አጋቢና ሚስጢራዊነት በገዥው ሰፈር ይስተዋላል:: በተለይ የብልጽግናው ኦዴፓ ከእግር ጥፍሩ እስከ እንጥሉ በኦነግ ሲምፐታይዘሮች መጠቃቱን የሚያሳይ ምልክት ለማግኘት ምርመራ አያስፈልገውም:: መጠቃት ብቻ ሳይሆን ተወሯል ባዩም ብዙ ነው::  

 የመራራ/ጁሃር ኦፌኮም የሕወሃት ሕልውና ጨርሶ መጥፉቱን በስጋት የሚመለከት ነው:: ኦፌኮ ታክቲካል አጋር ለመሆኑ ደፍሮ ይፉዊ መግለጫ ባይሰጥም የፖለቲካ ርዕዮቱ ተጋሪ ነው:: በቅርቡም በሰጠው መግለጫ የሕወሃትን የክህደት ጦርነት ለማውገዝ አልፈለገም:: እንዲያውም ከሰሜኑ ወሳኝ ጦርነት ይልቅ

በሌሎች የሃገሪቱ ክፍሎች ላይ ትኩረት በመስጠት የሕወሃትን ጉዳይ ባላየ ማለፍን መርጧል:: ይህና ሌሎች ሁኔታዎች ተጨማምሮ የኦሮሞው ኤሊት የሕወሃት ሌጋሲን በሌላ ግልባጭ ጥገናዊ የዘውግ ፖለቲካ የማስቀጠል ፍላጎት እንዳለው ሁኔታዎች ይናገራሉ:: አፍቃሬ ሕውሃትነት በኦሮሞ የፖለቲካ ሰፈር በሸኔ በኩል የማያሻማ ምላሽ አግኝቷል::  

 በዘር ክልል የተደራጀው የፖለቲካ አወቃቀር ከሌንጮ ለታ እስከ ሽመልስ አብዲሳ ተቀባይነት ያለው ነው:: የኦዴፓም መርሆ የነበረውን ባለበት ከማስቀጥል የሚወጣ አይመስልም:: ጠቅላይ ሚንስትሩም ይህን አስተሳሰብ ይጋሩታል የሚል ግምት ከቅርብ ግዜ ወዲህ በስፉት ይነፍሳል:: ይህ ሊሆንም ላይሆንም ይችላል::  “እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል እንዲሉ” ሃቁ ሊገልጥ ቀኑ ለመቃረቡ መገመት ጠንቋይ አያስብልም:: 

 በጥቅሉ የኢትዮጵያ መዕከላዊ መንግስት ፣ ገዥው ፓርቲና ፣ ጠቅላይ ሚንስትሩ ሕወሃትንና የዘር ፖለቲካ ሌጋሲው ላይ ያላቸው አቋም ነጥሮ ሲወጣ የኢትዮጵያ ብሎም የአፍሪካ ቀንድ የፖለቲካ ሃይል አሰላለፍ ምን መሆን እንዳለበት ይወስናል:: የሕዝብና የኤሊቱም የትግል አቅጣጫ ጥራት ያገኛል:: በአንጻሩም የሕወሃት የሽብር ዘመቻ ተጋላጭ በሆኑት የአማራ አፉርና ኤርትራ የነበረው የቀውስና የጦርነት ሁኔታ ሌላ መልክ ይይዛል:: 

 የምዕራባውያን ተጽዕኖ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የፈጠረው የሕልም ተቃርኖ የሃገረ መንግስት አፈጣጠርና የታሪክ አረዳድ ግጭት; የኦሮሞ ኤሊት ለሕውሃት ሌጋሲ ያለው ታማኝነት ተጨማምሮ ሕወሃትን ተመልሶ የፖለቲካ ሕልውና ሊያቀዳጀው የሚችልበት ሁኔታ ሊመጣ ይችላል:: 

 ሕወሃት ተመልሶ የፖለቲካ ሕልውና አገኘ ማለት በተለይ ለአማራ አፉርና ኤርትራ ማባሪያ ለሌለው ቀውስ ተዳረጉ ማለት ነው:: ሕወሃት ዳግም ሕይወት ዘርቶ ሊቆም አይገባም:: ሕወሃት የሞት ነጋዴ የጭካኔ ንጉስ የቅጥረኝነት አውራ በመሆኑ ዳግም እድል አግኝቶ ሕዝባችን ማለቂያ ለሌለው መከራ እንዳይዳረግ በሚቻለውና በማንኛውም መንገድ ማስወገድ ለመላው ኢትዮጵያዊ በተለይም ለአማራ አፉርና ኤርትራ አማራጭ የሌለው ምርጫ ነው:: 

 የትግሬ ወራሪ ዘራፊና ሽብርተኛ ሃይል በድንበር ተጎራባች ከሆኑት አማራ አፉርና የኤርትራ ሕዝብ ትላንት ካደረሰባቸው በላይ ለዳግም ጥቃት እንዳይጋለጡ የተናበበና በጥምር የሚመራ የጸጥታ ትብብር ከወዲሁ ሊያስቡበት ይገባል:: ምሁራን የማህበረሰብ አንቂዎችና መላው ሕዝቡ አማራጭ የትግል መንገዶችን በግዜ መፈተሽ ይኖርበታል:: በተለይም የኤርትራ ሕዝብና መንግስት የአማራና የአፉር ማህበረሰብ መተባበር ከቻለ አይደለም ሕወሃትንና ቡችሎቹን ማንኛውንም ምድራዊ ሃይል መቋቋም ይችላል:: 

 ይህ የቢሆን እይታና የፖለቲካ ትንተና በግዜ በቂ ትኩረትን አግኝቶ ዝግጅት እንዲደረግበት ለማስገንዘብ ነው:: አበው “አይሆንምን ትተህ ይሆናልን ጠብቅ” እንዲሉ አሸዋ ላይ የቆመ መንግስትንና ሚናውን ያለየ መሪንተከትሎ ለአደጋ ከመጋለጥ አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ አድርጎ መጠበቅ ትርፍ እንጂ ኪሳራ አይኖረውም:: 

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!! 

ድል ለሕዝባችን!!
_
በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,705FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here