spot_img
Saturday, September 30, 2023
Homeዜናበቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት 10 ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ ተወሰነ

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት 10 ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ ተወሰነ

advertisement

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

በመጪው መስከረም ራስ ገዝ የሚሆነውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ሳይጨምር በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታትም 10 ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ መንግሥት አቅጣጫ ማስቀመጡን የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

መንግስት ያስቀመጠውን አቅጣጫ በተመለከተ መግለጫ የሰጡት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ፒኤችዲ) ናቸው።

ሚኒስትር ዲኤታው ትግበራው ለትምህርት ጥራት፣ በተቋማቱ መካከል የትብብር እና የፉክክር መንፈስ በማምጣት ልሕቀትን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ጠቁመው በዚህ ምክንያትም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲን ዕውን ለማድረግ እንደሚረዳ ገልፀዋል።

ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ ሲሆኑ ተወዳድረው ከውጭም ሀብት ያገኛሉ፤ ከአገር ውስጥ ከንግዱም ማኅበረሰብ በምርምርና በማማከር ገቢ ያስገባሉ፤ ብቁ ተማሪ ስለሚያወጡ ከመንግሥትም ተጨማሪ በጀት ያገኛሉ ነው ያሉት ሚኒስትር ዲኤታው።

ውድድሩ ልህቀት እንደሚያመጣ እና በአገር ውስጥ ሳይገደብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ ተቋም መፍጠር እንደሚያስችልም ተመላክቷል።

ለመምህራኖቹ የተሻለ የደመወዝ ክፍያ እና ጥቅማ ጥቅም አሟልተው እንዲቀጥሩ የሚያስላቸው ይሆናል፤ ለሚቀጥሯቸው መምህራንም እንደ አቅማቸው የሚከፍሉበት ዕድል ይሰጣቸዋል ብለዋል ዶ/ር ሳሙኤል ደስታ።

ሚኒስትር ዲኤታው “በዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሆነ ተቋም መፍጠር ያስፈልጋል፤ ዩኒቨርሲቲን በሰፈር አጥረነው መቀጠል የለብንም፤ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ በመሆኑም ራስ ገዝነት በጣም ወሳኝ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

__

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,705FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here