spot_img
Saturday, September 30, 2023
Homeአበይት ዜናየሸኔ የደቡብ ዞን ምክትል ሀላፊ በቦረና ዞን ሞያሌ ወረዳ መያዙን መንግስት ገለፀ

የሸኔ የደቡብ ዞን ምክትል ሀላፊ በቦረና ዞን ሞያሌ ወረዳ መያዙን መንግስት ገለፀ

advertisement

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

መንግስት አሸባሪ ሲል የሰዬመው ሸኔ የደቡብ ዞን ምክትል ሀላፊ የሚል ሀላፊነት የተሰጠው ተጠርጣሪ በቤት መኪና ወደ መሀል አገር ሲጓዝ በቦረና ዞን ሞያሌ ወረዳ መያዙን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል፡፡

የመምሪያው ኮሚኒኬሽን ረዳት ዲቪዥን ሀላፊ ኢንስፔክተር ግርማ ሹሚ ተጠርጣሪው መኪና ተኮናትሮ ወደመሀል አገር ለመግባት ተዘጋጅቶ መኪናውን በመጠባበቅ ላይ እንዳለ በሞያሌ ወረዳ ልዩ ስሙ ቦቆላ በተባለ ስፍራ መያዙን ተናግረዋል።

ተጠርጣሪው ከአዳማ ከተማ በተላከለት የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 B-37253 አአ በሆነ መኪና በመጓዝ ላይ እንዳለ በፖሊስ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ሐምሌ 30 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰአት አከባቢ ተይዟል ብለዋል፡፡

በቁጥጥር ስር የዋለው ተጠርጣሪ ቀድሞ የሚታወቅበትን ‘መሀመድ አሜ’ የሚለውን የመጠሪያ ስሙን አብዱ ኡመር ሁሴን በሚል ቀይሮ መታወቂያ በማሰራት ሲንቀሳቀስ እንደነበር ጠቁመዋል፡፡ ግለሰቡ “ከአሸባሪው የሸኔ ቡድን” ጋር ብቻ ሳይሆን አልሻባብን ከመሳሰሉ ከአለም አቀፍ አሸባሪዎች ጋር ግንኙነት እንዳለው የሚጠረጠር እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡

የቦረና ዞን ፖሊስ ተጠርጣሪውን ጭኖ የነበረውን መኪና ከነአሽከርካሪው በቁጥጥር ስር አውሎ ጉዳዩን በመከታተል ላይ እንደሆነ ተገልጿል።

__

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,705FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here