spot_img
Monday, May 29, 2023
Homeአበይት ዜናከምስራቃዊ የአማራ ክልል የተነሱ ተሳፋሪዎች አዲስ አበባ ለመግባት እንደሚንገላቱ ገለፁ

ከምስራቃዊ የአማራ ክልል የተነሱ ተሳፋሪዎች አዲስ አበባ ለመግባት እንደሚንገላቱ ገለፁ

- Advertisement -

መንግሥት በፀጥታ ሥጋት ምክኒያት የሚደረግ ፍተሻ ነው ብሏል

Ethiopian News _ Amhara _ August 9, 2022

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

ከሰሜንና ደቡብ ወሎ እንዲሁም ከዋግ ኽምራ ዞኖች ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ ተሳፋሪዎች ኦሮምያ ክልል ከተሞች ሲደርሱ “የአዲስ አበባ መታወቂያ አልያዛችሁም” በሚል ምክንያት ወደ መጡበት እንዲመለሱ መደረጋቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ገለፁ፡፡

ተሳፋሪዎቹ “የምንኖርበት እየታወቀ የማንኖርበትን ከተማ መታወቂያ እንድናመጣ መጠየቁ አግባብነት የለውም” ይላሉ፡፡ የአማራ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የተፈጠረው መጉላላት ከፀጥታ ጉዳይ ጋር የተያያዘ ቢሆንም አፈጻጸሙ ብዙሃኑን ተሳፋሪ ለእንግልትና ለአላስፈላጊ ወጭ የዳረገ እንደሆነ ጠቁሟል፡፡

ከኦሮምያ ክልል እስካሁን በጉዳዩ ላይ የተሰጠ ማብራሪያ የለም፡፡  በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሠጡት የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ሠላማዊት ካሣ ሁኔታው ከጥብቅ የፀጥታ ቁጥጥር ጋር የተያያዘ መሆኑን ተናግረዋል። መታወቂያ ለመሥራት የሚያስፈልጉትን ጨምሮ የተለያዩ ሰነዶች በህወሓት ተይዘው ከነበሩ የአማራ ክልል አካባቢዎች መወሰዳቸው ደግሞ ለጥብቅ ቁጥጥሩ መነሻ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አፈጻጸሙን በተመለከተ ግን ማሻሻያዎች መደረግ እንዳለባቸውና የደህንነት እና የፀጥታ መዋቅሩን ማጥራት እንደሚያስፈልግም ዛሬ የወጣውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤት መግለጫ በመጥቀስ አብራርተዋል።

__

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር
፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,866FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here