spot_img
Wednesday, October 4, 2023
Homeዜናከ640 ሽህ በላይ የሚገመቱ የህክምና ማሽኖች ተሠርቀው ሊወጡ ሲሉ በቁጥጥር ስር ዋሉ

ከ640 ሽህ በላይ የሚገመቱ የህክምና ማሽኖች ተሠርቀው ሊወጡ ሲሉ በቁጥጥር ስር ዋሉ

advertisement

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

በደሴ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አገልግሎት የሚሰጡ የላቦራቶሪ እቃዎች ተሠርቀው ሊወጡ ሲሉ በጥበቃ ሰራተኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ዶክተር ሀይማኖት አየለ የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ገልጸዋል፡፡

ከወረራ በኋላ ለቆጠራ ታሽጎ የነበረው የላብራቶሪ ስቶር ክፍል ተከፍቶ 4 ማይክሮስኮፕ: 1 የኬሚስትሪ ማሽን ፕሪንተር 1የላብራቶረ ድቫይደር 5የበር ዶረሎክ ቁልፍ ተሠርቀው ሊወጡ ሲል ተይዟል፡፡

እንደ ዶክተር ሀይማኖት ገለጻ ከዚህም በፊት መድሀኒት ተሠርቆ ሊወጣ ሲል በቁጥጥር ስር ውሏል ብለዋል፡፡ የመድሀኒት ኦዲት ስራ ተሰርቶ 600ሽህ ብር በጉድለት የተገኘ ሲሆን አጥፊውን በዲስፕሊን እርምጃ በመውሰድ የተባረረ ሲሆን ጉድለቱን የክፍሉ ባለሙያዎች እንዲከፍሉ ተደርጎል፡፡

ሆስፒታሉ አሰራሩን እያሻሻለ ሲመጣ ልዩ ልዩ ያልተገባ ጥቅም የለመዱና የሚፈልጉ አካላት ወደ ስርቆትና ስም የማጥፋት ዘመቻ ገብተዋል ሲሉ ዶክተር ሀይማኖት ገልጸዋል ሲል የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ዘግቧል።

__

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,733FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here