spot_img
Monday, May 29, 2023
Homeአበይት ዜናከአማራ ክልል አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ወደ ምስራቅ አማራ...

ከአማራ ክልል አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ወደ ምስራቅ አማራ የሚጓጓዙ መንገደኞች እንግልት እየደረሰባቸዉ መኾኑን ተናገሩ

- Advertisement -

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

ከተለያዩ የአማራ ክልል አካባቢዎች ተነስተዉ ደብረ ብርሃንን አቋርጠዉ ወደ አዲስ አበባ የሚጓጓዙ መንገደኞች እንግልት እየደረሰባቸዉ ስለመሆኑ ሰሞኑን በተደጋጋሚ ሲገልፁ ተደምጧል፡፡

ዛሬ ደግሞ ጫጫ ከተማ ላይ መንገድ በመዘጋቱ ወደ አዲስ አበባም ሆነ ከአዲስ አበባ ወደ ምስራቅ አማራ የሚመጡ በርካታ ተሽከርካሪዎች ቆመዋል። ተጓዦችም ለእንግልት ተዳርገዋል።

መንገዱ የተዘጋው ሰሞኑን ወደ አዲስ አበባ በሚጓዙ መንገደኞች ላይ በኦሮሚያ ክልል ከተሞች ሲደርስ በነበረው እንግልት ቁጣ ውስጥ በገባው የጫጫና አካባቢው ማህበረሰብ መሆኑን በስፍራው የሚገኙ ምንጮች ገልፀዋል። ደብረ ብርሃንም ላይ በተመሳሳይ መንገድ ተዘግቷል። የደብረ ብርሃን ዞናል መናሃሪያ አገልግሎት መስጠት አቁሟል፡፡

የሰሜን ሸዋ ዞን ትራንስፖርት መምሪያ ኀላፊ ሲሳይ ወልደአማኑኤል፤ መንገደኞችና አሽከርካሪዎች እስከዛሬ ተደጋጋሚ ቅሬታ ሲያነሱ መቆየታቸዉን አስታዉሰዉ ለችግሩ መፍትሄ ባለመቀመጡ አሁን ጉዳዩ የከፋ ገፅታ መላበሱን ገልጸዋል፡፡

__
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር
 ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,864FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here