
ቦርከና
ጀማል ሰይድ
የጉራጌ ዞን የፀጥታ ኮማንድ ፖስት አስተባባሪ ሌተናንት ኮሎኔል ፈጠነ ፍስሃ እንደገለፁት የጉራጌ ዞን ምክርቤት በክላስተር የመደራጀት ምክረ ሀሳብ ላይ በጥልቀት ከተወያየበት በኋላ በአብላጫ ድምጽ ውድቅ አድርጓል። የዞኑ ምክርቤት በክልል የመደራጀት ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ ህብረተሰቡ ደስታውን በተለያየ መንገድ እየገለጸ ሲሆን ህብረተሰቡ ደስታውን ሲገልጽ በሰላማዊ መንገድ መሆን እንዳለበት አስተባባሪው አሳስበዋል።
የዞኑ ህዝብ ሰላም ለማደፍረስ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ሊኖሩ ስለሚችሉ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ብለዋል። በቀጣይ የዞኑ ምክርቤት ያጸደቀው በክልል የመደራጀት ውሳኔ መንግስት ምላሽ እስኪሰጥበት ድረስ የዞኑ ህዝብ በትዕግሥት መጠበቅ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የዞኑ ህብረተሰብ የአካባቢውን ሰላም ሲያስጠብቅ እንደነበረ የገለጹት አስተባባሪው እስካሁን በነበረን ቆይታ ከህዝቡ ጋር ተግባብተን ስንሰራ ነበር ። በቀጣይም የአካባቢውን ሰላም እንደሚያስጠብቁ እምነታቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም የህብረተሰቡን ሰላም ለማወክ የሚንቀሳቀሱ የውስጥና የውጭ ጠላቶች በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ሁሉም የዞኑ ነዋሪዎች ለጸጥታ አካላት መረጃ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል ሌተናንት ኮሎኔል ፈጠነ ፍስሃ ።
ምንጭ:-የጎራጌ ዞን ኮምንኬሽን
__
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena