spot_img
Monday, October 2, 2023
Homeዜናፌዴሬሽን ምክር ቤት፤ በደቡብ ክልል አደረጃጀት ጉዳይ ላይ በሚቀጥለው ሳምንት አስቸኳይ ስብሰባ...

ፌዴሬሽን ምክር ቤት፤ በደቡብ ክልል አደረጃጀት ጉዳይ ላይ በሚቀጥለው ሳምንት አስቸኳይ ስብሰባ ሊያካሄድ ነው

advertisement
አቶ አገኘሁ ተሻገር የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ሆነው በተሾሙበት እለት በመንግስት መገናኛ ብዙሃን የተለቀቀ


ጀማል ሰይድ

ቦርከና

መደበኛው ጉባኤውን ከአንድ ወር በፊት ያደረገው የፌዴሬሽን ምክር ቤት፤ በደቡብ ክልል አደረጃጀት ጉዳይ ላይ ውሳኔ ለማሳለፍ አስቸኳይ ስብሰባ ሊያካሄድ ነው። በሚቀጥለው ሳምንት ረቡዕ ነሐሴ 11፤ 2014 ለሚደረገው ለዚሁ አስቸኳይ ስብሰባ ጥሪ እንደተደረገላቸው ነገሩኝ ያላቸውን ሁለት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት ጠቅሶ “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘግቧል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ተረፈ በዳዳ፤ ምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባውን በመጪው ረቡዕ እንደሚያካሂድ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል። አቶ ተረፈ ምክር ቤቱ “ከደቡብ ክልል ጋር ተያይዞ የሚወስናቸው ውሳኔዎች ይኖራሉ” ሲሉ ስብሰባው የተጠራበትን ምክንያት ገልጸዋል።

በደቡብ ክልል የሚገኙ አስር ዞኖች እና ስድስት ልዩ ወረዳዎች፤ በሁለት የተለያዩ ክልሎች የመደራጀት ጥያቄያቸውን ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ሐምሌ 28፤ 2014 ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ጽህፈት ቤት አስገብተዋል። ጥያቄዎቹን የያዙ ሰነዶች ርክክብ ስነ ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር፤ “የፌዴሬሽን ምክር ቤት በጥያቄው ላይ ውይይት አካሄዶ፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ውሳኔ ወስኖ የሚያሳውቅ ይሆናል” ብለው ነበር።

__
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,723FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here