spot_img
Sunday, September 24, 2023
Homeአበይት ዜናባልደራስ ፕሬዝዳንቱ እስክንድር ነጋ “የመታፈን አደጋ ደርሶባቸዋል” የሚል እምነት እንደሌለው አስታወቀ   

ባልደራስ ፕሬዝዳንቱ እስክንድር ነጋ “የመታፈን አደጋ ደርሶባቸዋል” የሚል እምነት እንደሌለው አስታወቀ   

advertisement
ባልደራስ
የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ አመራሮች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት


ጀማል ሰይድ
  
ቦርከና                                                                                                      

የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ዛሬ ሰኞ ነሐሴ 9/2014 በጽህፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ በቅርቡ ከፓርቲው ፕሬዝዳንትነት መልቀቃቸውን ያሳወቁት አቶ እስክንድር ነጋን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል። 

የባልደራስ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አምሃ ዳኛው፤  የፓርቲው አመራሮች አቶ እስክንድር ስላሉበት ሁኔታ ከእርሳቸው በቀጥታ መረዳት ባይችሉም፤ “የመታፈን አደጋ ደርሶባቸዋል” የሚል እምነት እንደሌላቸው አስታውቀዋል። 

“ባልደራስ እስክንድርን ከድቷል ወይስ እስክንድር ነው ባልደራስን የከዳው?” በሚል ከጋዜጠኞች ለቀረበ ጥያቄ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ዶ/ር በቃሉ አጥናፉ በሰጡት ምላሽ፤ “እስክንድርን ሊከዳ የሚችል ፓርቲ አይኖረንም። የተሰበሰብነውም እስክንድር ብለን ነው” ብለዋል። “እስክንድርን ያህል የጽናት ተምሳሌት፤ ባለበት የፖለቲካ ጫና ምክንያት ከፖለቲካ ትግሉ ገሸሽ አለ ማለት፤ ፖለቲካው ላይ ያለው ተጽዕኖ ምን ያህል ከባድ እንደሆነ መረዳት [የሚያስችል ነው]” ሲሉም ተናግረዋል ሲል ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።  

__
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,682FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here