spot_img
Tuesday, October 3, 2023
Homeአበይት ዜናአካባቢያዊ ምርጫን ማከናወን የሚያስችል ውይይት እየተካሄደ ነው  

አካባቢያዊ ምርጫን ማከናወን የሚያስችል ውይይት እየተካሄደ ነው  

advertisement

ጀማል ሰይድ  
ቦርከና  

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አካባቢያዊ ምርጫን ለማከናወን የሚያስችለውን ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር እያደረገ ነው ።  

በኢትዮጵያ ለአምስተኛ ጊዜ በሚደረገው አካባቢያዊ ምርጫ ለሚደረገው ዝግጅት ቦርዱ ያስጠናውን ጥናት ተከትሎ ነው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሌሎችም 160 የሚሆኑ ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ የሆኑበት ውይይት እየተካሄደ ያለው። የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ አካባቢያዊ ምርጫ አስፈላጊቱ እጅግ ጉልህ መሆኑን ተናግረዋል። 

አካባቢያዊ ምርጫን ለማከናወን እና ትክክለኛ ልምምድን ከአዳጊ ሀገራት ለመማር ውይይቱ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። ምርጫውን በየክልሎቹ ለማስፈፀም ፣ የሚገጥሙ ችግሮች እና ሊኖሩ የሚችሉ የህግ ማሻሻያዎች ለውይይቱ ግብዓት እንዲሆኑ መድረኩ መዘጋጀቱንም ጠቅሰዋል። 

በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚደረገው አካባቢያዊ ምርጫ ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ወረዳ እና ዞን ድረስ ዜጎች ተወካዮቻቸውን በመምረጥ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን የሚያዳብሩበት ነው  ብለዋል። በአካባቢያዊ ምርጫ እና አካባቢያዊ የመንግስት አስተዳደርን በተመለከተም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፌደራሊዝም ጥናት ማዕከል ጥናት በዶክተር ዘመላክ አየለ ቀርቧል። 

 በዚህ ወቅትም አካባያዊ ምርጫ ውክልናን ለማስፋት እና በፖለቲካ ሂደት ውስጥ ምህዳሩን ለማስፋት እና ውድድርን ለመፍጠር በከፍተኛ ደረጃ እንደሚረዳ የሀገራትን ተሞክሮ በማቅረብ አስረድተዋል።

__

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,723FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here