spot_img
Saturday, September 23, 2023
Homeአበይት ዜናወደ ዘጠኝ ሺህ የሚጠጉ እና በአፋር ክልል መዲና ሰመራ ውስጥ ታስረው የነበሩ...

ወደ ዘጠኝ ሺህ የሚጠጉ እና በአፋር ክልል መዲና ሰመራ ውስጥ ታስረው የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች ተለቀቁ

advertisement

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

ሰመራ ውስጥ በሚገኝ የማቆያ ካምፕ ውስጥ ያለፈቃዳቸው ተይዘው ከነበሩት መካከል የተወሰኑት በአውቶብሶች እና የደረቅ ጭነት መኪኖች ተሳፍረው ወደ ቀደመ መኖሪያቸው እየተወሰዱ እንደሆነ ትናንት ነሐሴ 10/2014 ዓ.ም. ለቢቢሲ ገልጸዋል።

በሺዎች የሚቆጠሩት የትግራይ ተወላጆች ከአፋሯ አብኣላ ተይዘው ወደ ሰመራ 

መዘዋወራቸውን ለቢቢሲ ገልጸው ነበር።

ከስምንት ወራት እስር በኋላም ወደ አብኣላ እየተመሰሉ መሆኑን ተናግረዋል።

በሰመራ ተይዘው የነበሩ የትግራይ ተወላጆችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ሰዎቹ “በብሔራቸው” ምክንያት ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ ተይዘዋል ብሎ ነበር።

የትግራይ ተወላጆቹ ወደ ቀደመ የመኖሪያ ስፍራቸው እንዲመለሱ ሲያመቻች የነበረው የተባበሩት መንግሥታት በበኩሉ ሰዎቹን “የአገር ውስጥ ተፈናቃይ ሲል” ገልጿቸዋል።

በሰመራ ያለ ፍላጎታቸው ተይዘው ከነበሩ ሰዎች መካከል ቃላቸው ለቢቢሲ የሰጡ፤ ከመኖሪያቸው በአፋር ክልል ፀጥታ አስከባሪ ኃይል አባላት ተይዘው ወደ ሰመራ መወሰዳቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በበኩላቸው ሰዎቹ ከነበሩበት ቦታ እንዲዘዋወሩ የተደረገው ግጭት መስፋፋቱን ተከትሎ ለራሳቸው ደኅንነት ነው ብለው ነበር።

በሺዎች የሚቆጠሩት እዚህ ሰዎች ለወራት ተይዘው በቆዩበት ካምፕ ውስጥ የምግብ እና ሌሎች አገልግሎቶች ችግሮች እንደነበሩባቸው የተናገሩ ሲሆን፣ ለተለያዩ የጤና ችግሮች ተጋልጠው መቆየታቸውን ተናግረዋል።

ሁለት ዓመት ሊሞላው የተቃረበው ጦርነት ከትግራይ ጠነስቶ ወደ አፋር ክልል ከተዛመተ በኋላ በርካታ ሰዎች ለመፈናቀል መዳረጋቸውን የረድኤት ድርጅቶች መግለጻቸው ይታወሳል።  

__
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,676FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here