spot_img
Saturday, September 30, 2023
Homeአበይት ዜና" የተሰራጨው ሀሰተኛ ወሬ ነው " - የሶማሌ ክልል መንግስት

” የተሰራጨው ሀሰተኛ ወሬ ነው ” – የሶማሌ ክልል መንግስት

advertisement
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሙስጠፌ ሙሁመድ
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሙስጠፌ ሙሁመድ

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

የሶማሌ ክልል መንግስት በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ  በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ሙስጠፌ ሙሁመድ ላይ ” የግድያ ሙከራ ተደረገባቸው ” በሚል በማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው ብሏል፡፡ የክልሉ መንግስት ” በትላንትናው እለት በተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች በሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሀመድ ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ ተብሎ የተሰራጨው ዜና ከእውነት የራቀ ሀሰተኛ ወሬ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን። ” ብሏል።

በትላንትናው ዕለት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደርን የሚመለከቱ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር። አንደኛው ይኸው ” የግድያ ሙከራ ተደረገባቸው ” የሚለው ሲሆን የግድያ ሙከራ ተደረገባቸው የተባለው ለስራ ጉዳይ ” ቢኪ ” የሚባል ቦታ በሄዱበት ወቅት ነው።

ሌላኛው ደግሞ ፤ ርዕሰ መስተዳደር ሙስጠፌ ወደዚሁ ” ቢኪ ” የተባለ ስፍራ በሄዱበት ወቅት ወጣቱን ጨምሮ ፤ ህብረተሰቡ በመቆጣቱ ከፍተኛ ተቃውሞ እንደነበር ፤ ድንጋይም እስከመወርወር የደረሰ ክስተት እንደተፈጠረ የሚገልፅ መረጃ ተሰራጭቷል።

የክልሉ መንግስት ፤ በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ላይ ” የግድያ ሙከራ አልተደረገባቸውም ውሸት ነው ” የሚል መግለጫ ቢሰጥም በተመሳሳይ ሰዓት ስለተሰራጨው የ ” ቢኪ ” ከፍተኛ ተቃውሞ በተመለከተ እንዲሁም ርዕሰ መስተዳደሩ ወደ ተባለው ስፍራ አቅንተው እንደሆነ ፤ ሄደውስ ምን እንደተፈጠረ የገለፀው ነገር የለም ፤ ማስተባበያም አልሰጠም። 

ዘግየት ብሎ ከሲቲ ዞን የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በደረሰን መልዕክት ትላንት ፕ/ት ሙስጠፌ ቢኪ ላይ ተቃውሞ ገጥሟቸው እንደነበር፤ የፀጥታ ኃይሎች ሁኔታውን እንደተቆጣጠሩ፣ የግድያ ሙከራ የተባለው ግን ትክክል እንዳልሆነ ገልፀዋል።

__
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,705FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here