spot_img
Monday, October 2, 2023
Homeዜናየፌደሬሽን ምክር ቤት በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ስር የሚገኙ 6...

የፌደሬሽን ምክር ቤት በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ስር የሚገኙ 6 ዞኖች እና 5 ልዩ ወረዳዎች ያቀረቡትን በጋራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመመሰረት ጥያቄ ላይ ተወያይቶ ሕዝበ ውሣኔ እንዲካሄድ ወሰነ

advertisement

ቀሪዎቹ የሀድያ ዞን፣ ሀላባ ዞን፣ ከንባታ ጠንባሮ ዞን፣ ጉራጌ ዞን፣ ስልጤ ዞን እና የም ልዩ ወረዳ በነባሩ ክልል ይቀጥላሉ ተብሏል

የፌደሬሽን ምክር ቤት

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት እያካሄደው ባለው አስቸኳይ ስብሰባ ከቀረበው የውሳኔ ሀሳብ አስቀድሞ በማንነት አስተዳደር እና የወሰን ግንባታ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኩል በደቡብ ክልል10 ዞኖ ችአቅርበው ስለ ነበረው በተናጠል እንደራጅ ጥያቄ እና ይህንኑ መሰረት በማድረግ ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ዝርዝር ቀርቧል፡፡

ሕዝበ ውሳኔ የሚያካሂዱት ፦

– የወላይታ ዞን፣

– የጋሞ ዞን፣ 

– የጎፋ ዞን፣

– የደቡብ ኦሞ ዞን፣ 

– የጌዴኦ ዞን፣

– የኮንሶ ዞን፣ እንዲሁም

– የደራሼ ልዩ ወረዳ፣ 

– የአማሮ ልዩ ወረዳ፣ 

– የቡርጂ ልዩ ወረዳ፣ 

– የአኧ ልዩ ወረዳ እና የባስኬቶ ልዩ ወረዳ ናቸው።

በዚህም የክልልነት ጥያቄ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ ስራዎች ሲከናወኑ ቢቆዩም በተለይም ባለፉት 3 ወራት ዝርዝር የዳሰሳ እና መነሻ ሃሳብ እንዲቀርብ መደረጉ ተመላክቷል፡፡

በመነሻ ሃሳቡ በወጡት እቅዶችውስጥ መሰረታዊ  ሃሳቦች ቀርበዋል፡፡በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት ጥያቄዎቹን የህዝብን ጥቅም በሚያስከበር መልኩ መልስ እንዲያገኙ ማድረግ  እና  ዞኖች ከተናጠል ይልቅ በክላስተር ቢደራጁ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ የሚኖረው መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

__
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,723FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here