spot_img
Sunday, September 24, 2023
Homeዜናሩስያ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን መንግሥት እያከናወነ ያለውን የሰላም አማራጭ እንደምትደግፍ ገለጸች

ሩስያ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን መንግሥት እያከናወነ ያለውን የሰላም አማራጭ እንደምትደግፍ ገለጸች

advertisement
የሩስያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ምክትል ዳይሬክተር ኢቫን ኒቺዬቭ
የሩስያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ምክትል ዳይሬክተር ኢቫን ኒቺዬቭ

ፎዚያ አህመድ
ቦርከና

መንግሥት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እያከናወነ ያለውን የሰላም አማራጭ እንደምትደግፍ ሩስያ አስታወቀች።

የሩስያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ምክትል ዳይሬክተር ኢቫን ኒቺዬቭ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙርያ በሰጡት መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈን እያከናወነ የሚገኘውን የሰላም አማራጭ ሩስያ በብርቱ ትመለከተዋለች ብለዋል።

በተለይም መንግስት በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል አስቀድሞ የወሰዳቸውን የተናጠል ተኩስ አቁም፣ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅን ማንሳት፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋምና የሰብኣዊ ድጋፍ በተሻለ ሁኔታ እንዲዳረስ ያደረገውን ሰፊ እንቅስቃሴ ሩስያ በአበረታችነት ትወስደዋለች ነው ያሉት። በትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በተመለከተ መንግስት የሚከተለውን የሰላም አማራጭና አካታች የመፍትሔ አቅጣጫ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።

ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን፣ ተጨባጭ ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያዎች ለማድረግና ሰብኣዊ ድጋፉን ለማሳለጥ የሚያስችለውን የሰላም አማራጭ የሩስያ መንግስት እንደሚደግፈው አስታውቀዋል።

“ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ” በሚል በአፍሪካ ሕብረት በኩል የሚከናወነውን የሰላም አማራጭ የሩስያ መንግስት ይደግፈዋል ሲሉ ነው ያስታወቁት።

__

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,682FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here