spot_img
Monday, May 29, 2023
Homeዜናበአማራ ክልል ደብረ ብርሃን ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች የምግብ መመረዝ ገጠማቸው

በአማራ ክልል ደብረ ብርሃን ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች የምግብ መመረዝ ገጠማቸው

- Advertisement -
በአማራ ክልል

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

ከኦሮሚያ ክልል ተፈናቅለው በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የተለያዩ አካባቢዎችና በደብረ ብርሃን ከተማ የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች ለከፋ ጉዳትና እንግልት እየተጋለጡ መሆናቸው በተለያዬ ጊዜ ሲገለፅ ቆይቷል። ተፈናቃዮቹ መንግስት በአግባቡ ርዳታ እያደረገልን አይደለም ሲሉም በተደጋጋሚ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

 በተለያዩ መጠለያዎች የሚገኙት እነዚህ ተፈናቃዮች አሁን ካለባቸው ዘርፈ ብዙ ችግር ባሻገር፣   በአንድ ክፍል ውስጥ በተጨፋፈቀ መንገድ ለመኖር መገደዳቸው ለተለያዩ የጤና ችግሮች እንዲጋለጡ አድርጓቸዋል። ከሰሞኑም በደብረብርሃን ከተማ ወይንሸት ካምፕ ከሚገኙ ተፈናቃዮች 117 የሚሆኑት በምግብ መመረዝ መታመማቸው ተገልጿል።፡፡

የደብረ ብርሃን ከተማ ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ በቀለ ገብሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት ነሀሴ 15 ቀን 2014ዓ.ም በወይንሸት መጠለያ ካምፕ ውስጥ ከሚገኙ ተፈናቃዮች ውስጥ ለ3 መቶ ተፈናቃዮች የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም መካሄዱን ገልጸው ከተመገቡት ውስጥ 117ቱ መታመማቸውን አስረድተዋል፡፡ ሓላፊው ችግሩ እንደተከሰተም የከተማው አመራሮች፣የጸጥታ መዋቅር አካላትና የጤና ባለሙያዎች ባደረጉት ርብርብ የታመሙትን ወገኖች በፍጥነት ደብረ ብርሃን ሪፈራል ሆስፒታል፣04 ጤና ጣቢያ፣አየር ጤና፣ እና ጠባሴ ጤና ጣቢያዎች በመውሰድ እንዲታከሙ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል፡፡

በተደገው ጥረትና ርብርብ ታመው ከነበሩት ውስጥ 1 መቶ 16ቱ ወደ መጠለያ ጣቢያቸው መመለሳቸውን አረጋግጠው አንድ ሰው ግን አሁንም ህክምናውን እየተከታተለ እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡

ከምግቡ ጋር ተያይዞ ለተፈጠረው ችግር መንስዔው ምን እንደሆነ ለማወቅ ለደብረብርሃን ሪፈራል ሆስታል ናሙናው ተሰጥቶ በምርመራ ላይ እንደሚገኝ ያስረዱት አቶ በቀለ ውጤቱ እንደደረሳቸው ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ አሳውቀዋል፡፡ የችግሩን መንስዔ ውጤት እንደደረሰ ትክክለኛውን መራጃ በድጋሚ ይፋ እስከሚደረግ ድረስ ህብረተሰቡ በትዕግስት እንዲጠባበቅ ሲሉ የመምሲያ ሃላፊው ለደብረ ብርሃን ከተማ ኮሚኒኬሽን ተናግረዋል።

ተፈናቃዮቹ አሁን ያሉበት መጠነ ሰፊ ችግር እንዳለ ሆኖ የቀጣይ እጣፈንታቸው በውል አለመታወቁ ጉዳዩን አሳሳቢ ያደርገዋል።

__
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,866FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here