spot_img
Saturday, September 23, 2023
Homeዜናየደቡብ ወሎና ምዕራብ ጎጃምና  ዞኖች ለሁለት እንዲከፈሉ የአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት...

የደቡብ ወሎና ምዕራብ ጎጃምና  ዞኖች ለሁለት እንዲከፈሉ የአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ውሳኔ ማሳለፉን የአማራ ክልል ምክር ቤት አስታወቀ

advertisement

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

ሁለቱ ዞኖችን ለመክፈል ያስፈለገው በሕዝብ ጥያቄ መሆኑም ተመልክቷል። ነዋሪዎቹ የዞኖቹ መከፈል መልካም አስተዳደርንና ልማትን ያመጣል ይላሉ።

በአማራ ክልልም ሁለት ዞኖች የእንከፈል ጥያቄ አቅርበው የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ጥያቄውን ተቀብሎ ዞኖቹ እያንዳንዳቸው ለሁለት እንዲከፈሉ መወሰኑን የክልሉ ምክር ቤት ዐስታውቋል። የክልሉ ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ አማረ ሰጤ ዛሬ ለዶይቼ ቬለ (DW) አንዳመለከቱት በደቡብ ወሎ ዞን ስር ከነበሩ ወረዳዎች መካከል አብዛኛዎቹ አዲስ በሚደራጀው ዞን ውስጥ ተካትተዋል። ሰሜን ጎጃም በሚል ከነባሩ ምእራብ ጎጃም ተለይተው የተዋቀሩት ደግሞ 7 ወረዳዎችና 3 ከተማ አስተዳደሮች ናቸው ብለዋል። 

ዶቼቬሌ ያነጋገራቸው  የደቡብ ወሎ ነዋሪው አቶ እሸቱ አሊ ዞኑ እጅግ ሰፊ በመሆኑ ለአስተዳደር አስቸጋሪ ሆኖ በመቆየቱ በመከፈሉ «ደስተኛ ነኝ» ብለዋል። 

«ሰሜን ጎጃም» በሚል ከተካተተው ዞን ውስጥ የይልማና ዴንሳ ነዋሪው አቶ ከፍ ያለው እንየው ከዚህ በፊት ወደ ምዕራብ ጎጃም ማዕከል ፍኖተ ሰላም ለመድረስ ከእርቀቱ አኳያ ከፍተኛ እንግልት ይደርስ እንደነበር አስታውሰው ዞኑ ለሁለት መከፈሉ ብዙ ችግሮችን ይፈታል ነው ያሉት፡፡ ፍትህ ፈላጊ አቅመ ደካሞች ከእርቀትና ከወጪ አኳያ ጉዳያቸውን ሳስፈፅሙ የቀሩ ብዙዎች እንደሆኑም አስተያት ሰጪው ጠቁመዋል። 

የዞን ይከፈልልን ጥያቄ ይዘው ሲከራከሩ ከነበሩ ኮሚቴዎች መካከል በምዕራብ ጎጃም ዞን የዱር ቤቴ ከተማ አስተዳደር ነዋሪው አቶ ውበት ጥላሁን ለጥያቄያቸው ምክንያት የሆነውን ጉዳይ ለዶቼ ቬሌ አስረድተዋል።

መስተዳድር ምክር ቤቱ የዞኖቹን የእንከፈል ጥያቄ አወንታዊ ምላሽ የሰጠ ቢሆንም በቅርቡ ከርዕሰ መስተዳድሩ ጽ/ቤት የወጣ ደብዳቤ እንዳመለከተው በአዲስ የተደራጁ ዞኖች በ2015 ዓ.ም የዝግጅት ምዕራፍ እንዲሆንና በ2016 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ እንዲገቡ አሳስቧል።

ነባሩ ምዕራብ ጎጃም 14 ወረዳዎችና 8 ከተማ አስተዳደሮች፣ ደቡብ ወሎ ደግሞ 20 ወረዳዎችና 9 ከተማ አስተዳደሮችን ያቀፉ መሆናቸውን ከየዞኖቹ የመንግስት ጉዳዮች ኮሙዩኒኬሽን መምሪያዎች የተገኘው መረጃ ያሳያል።
_

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,681FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here