spot_img
Wednesday, October 4, 2023
Homeዜናምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ተቀማጭነታቸውን አዲስ...

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የዲፕሎማቲክ ማኀበረሰብ አባላት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ገለፃ አደረጉ

advertisement
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር _ Ethiopia Diplomat _ News
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የተደረጉ ጥረቶችን በስፋት አብራርተዋል። 

በገለጻቸውም በመንግሥት ለሰብአዊ ድጋፍ ሲባል የተደረገውን የተናጥል ተኩስ አቁም ውሳኔ እና ያልተገደብ ሰብአዊ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል ለማስገባት የተደረጉ ጥረቶችን አብራርተዋል። 

መንግስት ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ የሰላም አማራጭ ዐብይ ኮሚቴ በማቋቋም ወደ ሥራ መግባቱንም አስታውሰዋል። 

መንግስት የሥስተኛ ወገን ስምምነት በተመድ ጽ/ቤት በመፈረም እንዲሁም ከዓለም ባንክ በተገኝ ድጋፍ የአደጋ ጊዜ እና የማገገሚያ ፕሮጀክት በትግራይ ክልል ተግባራዊ እንዲደረግ መስማማቱን ገልፀዋል። 

ይሁን እንጂ የህወሓት ቡድን መንግስት የወሰዳቸውን የሰላም አማራጮች ወደ ጎን በመተው ጦርነት መክፈቱን እና የሚደርሰውን እርዳታም ለጦርነት እያዋለው መሆኑን ገልፀዋል። 

ይህ ቡድን በአፍሪካ ሕብረት ማዕቀፍ የተጀመረውን የሰላም ጥረት በመግፋት ወደ ጦርነት መግባቱን ተናግረዋል። 

ዓለም አቀፉ ማኀበረሰብ ይህን ድርጊት በጽኑ እንዲያወግዝ እንዲሁም ቡድኑ ወደ ሰላም አማራጭ እንዲመጣ ግፊት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

መንግሥት በንጹኃን ዜጎች ላይ ተጨማሪ ጉዳት እና ጥፋት እንዳይደርስ ቅድሚያ በመስጠት አሁንም ለሰላም አራጭ ዝግጁ ነው ያሉት አቶ ደመቀ መኮንን፤ የአገሪቱን ሉዓላዊ የግዛት አንድነት እና የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ጨምረው መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል።

__

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,733FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here