spot_img
Saturday, September 23, 2023
Homeዜናታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከሀይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል በዓመት እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር...

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከሀይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል በዓመት እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ገቢ እንደሚያስገኝ ተገለጸ

advertisement
ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ _ ሕዳሴ ግድብ
ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ (የሕዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ)

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ የሚኖረውን አገራዊና ቀጣናዊ ፋይዳ አብራርተዋል።

የግድቡ ግንባታ ሙሉ ቡሙሉ ሲጠናቀ ከሀይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል በዓመት እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ገቢ ያስገኛል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከውሃ ብቻ እስከ 45 ሺሕ ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ማመንጨት የምትችል መሆኑን ጠቁመው የጂኦ ተርማል፣ የፀሐይ እንዲሁም የነፋስ ኃይል ማመንጨት የሚያስችል እምቅ ሃብት አላት ብለዋል።

በመሆኑም ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ በሌሎችም የልማት መስኮች ለቀጣናዊ የልማት ትስስር ትኩረት ሰጥታ እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በሀይድሮ ኤሌክትሪክ ሀይል ከፍተኛ እምቅ ሀብት በመያዝ ከአፍሪካ ሁለተኛዋ ሀገር ብትሆንም፤ ከውሃ ሀብቷ የሚገባትን ጥቅም ሳታገኝ መቆየቷን አንስተዋል። ግድቡ በሁለት ዓመት ተኩል እንዲጠናቀቅ እየሰራን ነው ያሉት ኢንጂነር ክፍሌ፤ በአሁኑ ወቅት ሁለት ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት መጀመራቸውን ጠቅሰዋል።

በቀጣይ ግንባታው ሙሉ ቡሉ ሲጠናቀቅ እና 11 ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት ሲጀምሩ ኢትዮጵያ በዓመት እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢ እንደምታገኝ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ያሏትን የውሃ ሀብትና ሌሎች የታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብት በማልማት ለሀገራዊ እድገትና ለቀጣናው የኢኮኖሚ ትስስር መጠናከር እንደምትሰራም አብራርተዋል ያለው ኢዜአ ነው፡፡

__

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,673FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here