spot_img
Saturday, September 30, 2023
Homeዜናየህወሃት ጦር ወደ ወልዲያ ከተማ እየቀረበ መሆኑን ነዋሪዎች ተናገሩ

የህወሃት ጦር ወደ ወልዲያ ከተማ እየቀረበ መሆኑን ነዋሪዎች ተናገሩ

advertisement

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

ወራሪው የህወሃት ቡድን ትናንት ከሰአት በሗላ የቆቦ ከተማን ከተቆጣጠረ በሗላ ፣ ዛሬ ረፋድ ላይ ወደ ወልዲያ ከተማ
እየተጠጋ መሆኑን የወልዲያ ነዋሪዎች ጠቁመዋል። የቦርከና ዘጋቢ ፣ የከተማዋን ነዋሪዎች በስልክ አናግሮ እንዳገኘው
መረጃ የህወሃት ጦር ከወልዲያ በቅርብ ርቀት ላይ የምትገኘውን የሮቢት ከተማን ተቆጣጥሯል።

የወልዲያ ከተማም ባለመረጋጋት ውጥ መሆኗ ተነግሯል። በሌላ በኩል፣ የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማው ሕዝብ
ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ እና ለጥምሩ ጦር ደጀንነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ዛሬ ጥሪ አቅርቧል።” የሀገር
መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖ እና ሚኒሻው እየተፋለሙ ነው ” ያለው የወልድያ ከተማ ” የአካባቢው
ማኅበረሰብ አካባቢውን ተረጋግቶ በመጠቅ ለጥምር ጦሩ የተለመደ ሁለተናዊ ደጀንነቱን አጠናክሮ ይቀጥል ” ሲል
ጥሪውን አቅርቧል። ከተማ አስተዳደሩ ” የጦርነቱ የፍልሚያ ቦታ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከራያ ሚዳ አልዘለለም ” ያለ
ሲሆን ሾልኮ ለማለፍና በወሬ ለመፍታት የተደረገው ስልትም እስካሁን አልሰመረም ብሏል።


የከተማ አስተዳደሩ ዛሬ መልዕክቱን ያሰራጨው የአካባቢውን ተጨባጭ ሁኔታ በአካላዊ እንቅስቅሴ ጭምር በማጣራት
መሆኑን አመልክቷል።

__

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,705FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here