spot_img
Monday, May 29, 2023
Homeአበይት ዜናየሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሁኔታ እና የመንግስት ማሳሰቢያ

የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሁኔታ እና የመንግስት ማሳሰቢያ

- Advertisement -
ማክሰኞ ደሴ የነበረው ሁኔታ በከፊል ይሄን ይመስል ነበር ( ፎቶ ጀማል ሰይድ)
ማክሰኞ ደሴ የነበረው ሁኔታ በከፊል ይሄን ይመስል ነበር ( ፎቶ ጀማል ሰይድ)

ቦርከና

የሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ህወሓት) ለሶስተኛ ጊዜ የቀሰቀሰው ጦርነት ስድስተኛ ቀኑን ይዟል :: ቡድኑ የቆቦን ከተማ ከተቆጣጠረ በኋላ ጦርነቱ ባብዛኛው በወልዲያ እና በቆቦ መካከል ባሉ ቦታዎች እየተካሄደ እንደሚገኝ የተለያዮ ምንጮች እየጠቀሱ ነው::

የመንግስት ወታደሮች እስካሁን በመከላከል ላይ የተመረሰተ ወጊያ እያደረጉ እንደሆነም ነው የተነገረው:: ምንም እንኳን ህወሓት ከተለያዮ አቅጣጫዎች “የህዝብ ማዕበል” በሚባለው የጦር ስልት ውጊያ የከፈተ ቢሆንም ባሰበው ፍጥነት ወደፊት መግፋት እንዳልቻለ ታውቋል::

ትላንት ከወልዲያ ከተማ ነዋሪዎች መካክል የተኩስ ድምጽ ይሰማ አንደነበረ የተናገሩ ነበሩ:: በዚያው ምክንያት ከተማዋን እየተው ወደ ደሴ ስደት የጀመሩም እንደነበሩ ተሰምቷል::

አፍቃሪ ህወሓት የሆኑ መገናኛ ብዙሃን እና የ “ማህበረሰብ አንቂዎች” ወልዲያ ከተማ በህወሓት ኃይሎች እንደተያዘ ማስወራት ከጀመሩ ሶስት ቀናት ያለፈ ሲሆን እንደ አልጀዚራ ያሉ የውጭ መገናኛ ቡዙሃን ጭምር የሃሰት መረጃውን በስፋት አሰራጭተውታል ::

ሆኖም የወልዲያ ከተማ ባለስልጣናት ዜናው ሃሰተኛ መሆኑን አስረግጠው ህዝቡ የደጀንነት ሚናውን ባግባቡ አየተወጣ ነው ፤ ነዋሪዎችም የእለት ተለት አንቅስቃሴያቸውን እያከናወኑ ነው በሚል መግለጫ ሰተዋል::

ይሄ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ የወልደያ ከተማ በኢትዮጵያ ሃይሎች እጂ አንዳለች እና ከወልደያ ከተማም በመስጋት ወተው የነብሩ የተከማዋ ነዋሪዎች መመለስ መጀመራቸውን የቦርከና ዘጋቢ ማረጋገጥ ችሏል::

ስለ ወልደያ ሁኔታ ሃሰተኛ ዜና ከተሰራጨ በኋላ በደሴ ከተማም ሰኞ ማምሻ ላይ እና ማክሰኞ ጠዋት ላይ በነዋሪዎች ላይ የተሰተዋለ የመረበሽ ስሜት እንደነበረ ታውቋል:: ሁኔታው አንዳንድ ነጋዴዎችን እቃ አንዲያሸሹ ያደረገ ሲሆን ከተማዋን በመልቀቅ ወደ አዲስ አበባ እና ባህር ጋር ጉዞ የጀመሩም እንደነበሩም ለማወቅ ተችሏል:: ነዋሪዎች ገንዘብ ከባንክ ለማውጣት ረዣዥም ሰልፎችም ይዘው ታይተዋል::

በደሴ ሙጋድ አካባቢ ባለ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ገንዘብ ለማውጣት የነበረው ሰልፍ በከፊል ይሄን ይመስላል (ፎቶ ጀማል ሰይድ )
በደሴ ሙጋድ አካባቢ ባለ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ገንዘብ ለማውጣት የነበረው ሰልፍ በከፊል ይሄን ይመስላል (ፎቶ ጀማል ሰይድ )

የወልዲያ ከተማ አመራሮች መግለጫ ከሰጡ በኋላ ሁኔታው ተረጋግቶ አብዛኛው ነዋሪ ወደ እለት ተለት ስራው አንደተመለሰም ዘጋቢያችን ከቦታው አድርሶናል::

ወደ ደሴ ገብተው የነበሩም የወልዲያ ነዋሪዎች መመለስ መጀመራቸው ታውቋል::

የዛሬ አመት ገደማ የህወሓት ቡድን ደሴን አና ወልዲያን ጨምሮ በርካታ የአማራ ክልል አና የአፋር ክልል ከተሞችን ተቆጣጥሮ መጠነ ሰፊ ኢኮኖሚያዊ አና ማህበራዊ ውድመት ማድረሱ ይታወሳል:: በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችም ህይወታቸውን አጥተዋል፤ በርካቶች ከመኖሪያ ቦታቸው ተፈናቅለው የሰቆቃ ህይወት መርተዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር የሆኑት ዶክተር ለገሰ ማክሰኞ ለት “የውስጥ ባንዳዎችና ታሪካዊ ጠላቶቻችን ተቀናጅተው የከፈቱብንን ዘርፈ ብዙ ጦርነት ሁሉም ዜጋ በኅብረ ብሔራዊ አንድነት መመከት አለበት” ሲሉ አሳስበዋል::

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድም ወደ አልጀሪያ አድርገውት የነበረውን የስራ ጉብኝት አገባደው ማክሰኞ እለት ወደ ሀገር መመለሳቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል ::

__

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,864FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here