spot_img
Wednesday, October 4, 2023
Homeዜና23 የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ተቋማት ዛሬ የሥራ ፈቃድ ያገኛሉ

23 የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ተቋማት ዛሬ የሥራ ፈቃድ ያገኛሉ

advertisement
ፎቶግራፉ የኢትዮጵያ ፕሬስ ደርጂት ነው

ጀማል ሰይድ
ቦርከና

በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ 46 የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን ተቋማት መካከል 23ቱ ዛሬ የሥራ ፈቃድ እንደሚወስዱ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አስታወቀ።

የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ሀገራዊ የምክክር መድረክ “የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ለአብሮነት እሴቶች መጠናከር” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሐመድ እድሪስ፤ ኢትዮጵያ በወጡ ፖሊሲና አዋጆቿ በብዙ ሀገራት ባልተለመደ መልኩ ዕውቅና መስጠቷን ገልፀው በዚህ መሰረት የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ለተደረገው የምዝገባ ጥሪ ፈጣን ምላሽ ተሰጥተዋል ብለዋል። 

በሃገሪቱ ካሉ 46 የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን መካከልም አሥፈላጊውን መረጃ ያሟሉት 23 ያህሉ ዛሬ ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ፈቃድ እንደሚቀበሉ ገልፀዋል።

የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ትኩረት የተሰጠው ሃይማኖቶች በሀገር ግንባታ የተጫወቱት ሚና የማይዘነጋ በመሆኑ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ የመንግስት ዋናው ፍላጎት የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ሕግና ሥርዓት አክብረው በሰላምና አንድነት ዕሴት ግንባታ ላይ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ነው ሲሉ አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጠቅላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በበኩላቸው፤ 93 በመቶ ያህል አማኝ ባለባት ሀገር የሚታየው የሰላም እጦትና የተለያየ ችግር ሃይማኖቶች ተገቢውን አሥተምህሮ ያለመስጠታቸው ምልክት መሆኑን ገልፀዋል።

ሆኖም አሁን በተፈጠሩ ምቹ ሁኔታዎች ሃይማኖቶች በሚዲያዎቻቸው የግብረ ገብነት ትምህር ላይ በትኩረት በመሥራትና ትውልዱን በመቅረፅ ወደመከባበር መመለስ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

__

በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,733FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here