
ቦርከና
የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ዛሬ “የትግራይ መንግስት ማዕከላዊ ኮማንድ” በሚል ስያሜ ባሰራጨው ጥሪ ልጂ አዋቂ እና ጭማግሌ ሳይባል ሁሉም ትግራይዋይ በሙሉ አቅሙ መክተት አና “ጠላቶቻችን” ሲል የጠራቸውን የኢትዮጵያ ጥምር ጦር እና የኤርትራ ጦር በብዙ ግንባር ክፈተውብናል ያለውን ወረራ ለመቀልበስ ሁለ ገብ ዝግጂት እንዲደረግ አዟል::
ራሱን “የትግራይ መንግስት” እያለ የሚጠራው እና የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአሸባሪነት የፈረጀው ቡድን በመግለጫው ላይ ተከፍቶብኛል ያለው ወረራ “ትግራዋይን ከምድረገጽ ለማጥፋት” እንደሆነ ገልጾ የጠላቶቻንን ህልም ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለማምከን እያንዳንዱ ትግራዋይ በጦርነቱ በሙሉ አቅሙ መሳተፍ አለበት ብሎኣል ::
በሌላ በኩል ደሞ በኢትዮጵያ እና ለኤርትራ ህዝብ ባቀረበው ጥሪ የጦርነቱ ተባባሪ እንዳይሆኑ ጠይቋል::
ለኤርትራኖች ባስተላለፈው መልዕክት የኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት የኤርትራን ህልውና “ከማይቀበሉ ኃይሎች” ጋር ትብብር ፈጥሮ የከፈተብንን ጦርነት እንዳይደግፉ ጥሪውን አስተላልፏል:: የኢትዮጵያን ህልውና የማይቀበሉ ያላቸውን ኃይሎች በስም ባይጠቅስም ጦርነት ከፍተውብኛል ያላቸው የኢትዮጵያ ሰራዊት ፋኖ እና የ ኤርትራ ሰራዊት መሆናቸውን በመግለጫው ጠቁሟል::
የኢትዮጵያንም ህዝብ በተመሳሳይ በተለይም ደሞ የአፋር አና የአማራን ህዝብ ልጆቹን ወደ ጦርነት እየላከ “የሳት ራት” እንዳያደርጋቸው ጥሪ አቅርቧል ::
ይህ ዜና አስከወጣበት ጊዜ ድረስ ድረስ ከህወሓት በስተቀር በሁሉም ግንባር ተከፍቷል ስለትባለው ውጊያ የሚያረጋግጥ ወይንም የሚያስተባብል ዘገባ አልወጣም::
ለሰላም ንግግር በመንግስት እና በዓል አቀፍ ደረጃ ጥረት እየተደረገ በነበረበት ሰዐት በነሃሴ አጋማሽ ላይ የህወሓት ቡድን የሶስተኛ ዙር ጦርነት በመክፈት ቆቦን መቆጣጠሩ እና በምዕራብም በኩል በሁመራ ጦርነት መክፈቱ ይታወሳል::
እስካሁን የ አዳርቃይ ከተማ በምዕራብ ግንባር ከህወሓት ኃይሎች ቁጥጥር ነጻ መሆኑ ከመሰማቱ በስተቀር መንግስት ስለ ጦርነቱ ዝርዝር መግለጫ ከመስጠት ተቆጥቧል::
ህወሓት ዛሬ ያወጣው የክተት ኣዋጂ ከታች በተያያዘው የድምጽ ፋይል ማዳመጥ ይቻላል::
(የድምጽ ፋይሉ የተገኘው ከትግራይ ቴሌቭዥን ነው )
__
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ