spot_img
Wednesday, October 4, 2023
Homeአበይት ዜናየፕሮፌሰር ወሰኔ ይፍሩን ከዚህ ዓለም መለየት አስመልክቶ ከዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት የተሰጠ...

የፕሮፌሰር ወሰኔ ይፍሩን ከዚህ ዓለም መለየት አስመልክቶ ከዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት የተሰጠ የሃዘን መግለጫ 

advertisement

ዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት 
ዋሽንግተን ዲሲ 

ዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት በእዉቁና ታላቁ ኢትዮጵያዊ ምሁር ፕሮፌሰር ወሰኔ ይፍሩ እረፍት የተሰማውን መሪር ሀዘን ለቤተሰብ ለአገር እና ለወገን ሁሉ ለመግለፅ ይወዳል:: 

ፕሮፌሰር ወሰኔ ይፍሩ ከልብ በሚወዷት አገራቸው ኢትዮጵያ እውነተኛ ለውጥ እንዲመጣ፤ ፍትህ እንዲሰፍን፤ እኩልነት በተግባር እንዲረጋገጥ ደከመኝና ሰለቸኝ ሳይሉ የተቻላቸውን ሁሉ ሲያደርጉ ነበር:: 

ሕገ-መንግስት በመደንገግ አማራውን በተለየ-መልኩ ለማዳካምብሎም ለማጥፋት እየተካሄደ ያለውን ፀረ አማራዊ መጠነ ሰፊ ዘመቻ በመረዳታቸው፤ አማራው የተጋረጠበትን አደጋ ተባብሮ እንዲመከት ሲያስተምሩ፣ አጥብቀውም ሲመክሩ ነበር። 

በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፤ በተንኮል የተሸረበው ጎሳንና ቋንቋን መሠረት ያደረገው ሕገ-መንግስት በአዲስ ሕገ-መንግስት እንዲለወጥ ብዙ ደክመዋል። ለጠቅላይ ሚንስትሩም ጥልቅና ሰፊ ደብዳቤ ልከው ነበር። 

በሚዲያ እየቀረቡም ሃሳባቸውን ለሕዝብ አቅርበዋል። 

ይህን አስተዋፅዖ ማንኛውም አማራ ብሎም ፍትሕና እኩልነት ናፋቂው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ሲያስታውሰውና ሲዘክረው ይኖራል። 

ፕሮፌሰር ወሰኔ ይፍሩ ብዙ መፅሃፍትን ጽፈው ለትውልድ መማሪያነት አስተላልፈዋል። ታሪካችንን ከስሩ እንድናውቅም ጥረት አድርገዋል። ለዚህም አስተዋጽዖአቸው እናመሰግናቸዋለን። 

በዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት ከምስረታው ጀምሮ በተለያዩ ኃላፊነቶች በንቃትና በትጋት ስለሰሩ አጥብቀን እናመሰግናለን። ዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት፤ ፕሮፌሰር ወሰኔን የመሰለ ትልቅ ምሁር ማጣቱ ከባድ ሀዘን ነው፡፡ ነገር ግን የሚገባውን በመፅሃፍ ስላስተላለፉልን በዚህ ስራቸው ስንዘክራቸውና ስራዎቻቸውን ለትውልድ ለማስተላለፍ ቃል እንገባለን፡፡ 

በመጨረሻም ለውድ ቤተሰባቸው፤ ዘመድ ጓደኞቻቸው፤ የስራ ባልደረቦቻቸው እንዲሁም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን እግዚአብሔር መፅናናቱን እንዲሰጣችሁ እንለምናለን። 

ዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት 
ዋሽንግተን ዲሲ 

Professor Wosene Yifru

__

በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena 
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,733FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

1 COMMENT

  1. መቸ? እንዴት? የት? ሞቱ፤ የት ተቀበሩ? ቤተ ሰብ አላቸው? ፕሮፌሰርነታቸው በየትኛው ትምህርት ቤት ነው? ጨርሶ ትዝም አላላችሁም! አይ ጋዜጠኛነት!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here