spot_img
Saturday, April 1, 2023
Homeነፃ አስተያየትአደገኛው የከተማ ላይ ከተማ ምስረታ ፕሮጀክት

አደገኛው የከተማ ላይ ከተማ ምስረታ ፕሮጀክት

- Advertisement -
ከተማ

ከመርሐጽድቅ መኮንን አባይነህ

ከግማሽ ክፍለ-ዘመን አስቀድሞ በባእዳን ቅኝ ገዢዎች ሴራ የተወጠነውና በህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ) (ህ.ወ.ሀ.ት) ተልእኮ አስፈጻሚነት የተመራው ነገደ-አማራን አንገት የማስደፋቱና፣ ከተቻለም ህልውናውን ከምድረ-ኢትዮጵያ ጨርሶ የማጥፋቱ ፕሮጀክት በመንግሥት ሥልጣን ላይ የሚገኘውን የብልጽግና ፓርቲ የኦሮምያ ክንፍ ጨምሮ በተለያዩ ጊዜያት ተቋቁመው በኦሮሞ ስም በሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች አማካኝነት ዛሬም ተጠናክሮ መቀጠሉን እያስተዋልን ነው፡፡

በመሰረቱ ወያኔ በስሙ ከከለለለት አካባቢ ይልቅ የአማራው ማሕበረ-ሰብ የትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የዎርቅ ባድማዬ ነው በሚል መተማመን በመላዋ ኢትዮጵያ ከጽንፍ እስከአጽናፍ ነው በሰፊው ተሰራጭቶ የሚገኘው፡፡

ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት መነሻውን አማራ ክልል ያደረገና የዚህኑ ክልል መታወቂያ የያዘ ማንኛውም ዜጋ ሌላው ቀርቶ ወደመዲናዋ አዲስ አበባ እንኳ ድርሽ እንዳይል ግልጽ የሆነ እገዳ የተጣለበት ይመስላል፡፡

በፌደራሉ መንግሥት ኀላፊነት መተዳደራቸው ከናካቴው ተዘንግቶ መዲናዋን ከአማራ ክልል ጋር የሚያገናኙት ሁሉም አውራ ጎዳናዎች ጥርቅም ተደርገው ተዘግተዉበታል፡፡ ከዚህም የተነሳ በኦሮምያ ፖሊስና ጸጥታ ሀይሎች አስገዳጂነት ጉዟቸውን እያቋረጡ ወደኋላ እንዲመለሱ የሚደረጉት ወይም አውላላ ሜዳ ላይ የሚፈሱት ንጹሃን መንገደኞች ቁጥር ቀላል የሚባል አይደለም፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ እዚያው አዲስ አበባ ውስጥና በዙሪያዋ መዲናዋን ያለሀፍረት ለመሰልቀጥ ታስቦ በመደራጀት ላይ ከሚገኘው ከሸገር ከተማ ምስረታ ጋር በተያያዘ እንደሱሉልታ፣ ለገጣፎና ሰበታ ባሉት አነስተኛ የኦሮምያ አዋሳኝ ከተሞች ውስጥ የችግሩ ገፈት ቀማሾች እነርሱ ብቻ ናቸው ባይባልም በተለይ የአማራ ብሔር ተወላጆች የሰሯቸው መኖሪያ ቤቶችና ጥረው ግረው ያፈሯቸው ሀብቶች እየተመረጡ በዘፈቀደ በሚወሰድ እርምጃ ሲፈራርሱና ሲወድሙ ማየት እየተለመደ መጥቷል፡፡

እኛ እስከምናውቀው ድረስ ሸገር የሚለው ቃል አዲስ አበባችን ስትንቆለጳጰስ የምትጠራበት የቁልምጫ ስያሜ ነበር፡፡

ኦፊሴላዊ መቀመጫው በራሷ በአዲስ አበባ እንብርት ላይ እንዲሆን የተደረገውና እነአቶ ሽመልስ አብዲሳ የቆረቆሯትና እነዶ/ር ተሾመ አዱኛ በከንቲባነት የተሞሸሩባት ሸገር ግን ቀድሞ ነገር የሀገሪቱን መዲና በሁሉም አቅጣጫዎች አፍኖ ነዋሪዎቿን ለማስጨነቅና ዘላቂ ባለዋጋነቷን ለመቀነስ በስሌት ታቅዶ የተጠነሰሰ አደገኛ የከተማ ላይ ከተማ ምስረታ ፕሮጀክት መሆኑን እዚህ ላይ ልብ ይሏል፡፡

እንደእውነቱ ከሆነ በነባር ከተማ ወገብ ላይ ዙሪያውን እንደእባብ ተጠምጥሞ አዲስ የቁጩ ከተማን መቆርቆር ፈጽሞ ያልተለመደና እንግዳ የሆነ ነገር ነው፡፡

እነሆ ሸገር በተሰኘው ከተማ መልክኣ-ምድራዊ አፈና ምክንያት መዲናችን አዲስ አበባ ሀገረ-ሌሶቶን መስላላችኋለች፡፡ እንደሚታወቀው ዙሪያዋን በደቡብ አፍሪካ ሪፓብሊክ የተከበበችው ትንሽቱ አፍሪካዊት አገር ሌሶቶ የከባቢዋን አገር ፈቃድና ይሁንታ ካላገኘች በስተቀር ከውጪው አለም ጋር የመገናኘት እድል የላትም፡፡

አዱ-ገነትም ብትሆን ከእንግዲህ በኋላ በሸገር በኩል ካልሆነ በስተቀር ከሌሎች አቻ ከተሞችም ሆነ አጎራባች ክልሎች ጋር እንዳሻት የመገናኘት እጣ ፈንታ አይኖራትም፡፡

ይልቁንም ብዙዎቻችን ተስፋ እንደምናደርገው ሕገ-መንግሥቱ ተሻሽሎ በዚህ አገር በኦፊሴል የሚሰራበት መርዘኛ የብሔር ፖለቲካ አንዳች ለውጥ እስካልተደረገበት ድረስ ሸገር ቀስ በቀስ አዲስ አበባን ትውጣት/ትሰለቅጣት እንደሆነ ነው እንጂ አዲስ አበባ ትኩስ አቅም ኖሯት የሸገርን አደገኛ የብረት አጥር ሰብራ ትወጣለች ተብሎ በጭራሽ አይታመንም፡፡

በባንቱስታናይዜሽን ጋኔን ተይዘው አለቅጥ የሚቅበዘበዙት ስግብግብና ጽንፈኞቹ የኦሮምያ ገዢዎችም ከመነሻው የፈለጉት ይህንኑ የአዲስ አበባ ውድቀት ስለነበር ለጊዜውም ቢሆን ተሳክቶላቸዋል ለማለት ያስደፍራል፡፡

በርግጥ ፊንፊኔ የኛና የኛ ብቻ ናት ሲሉ ጉሮሯቸው እስኪነቃ ድረስ ጫፍ የረገጠ ጩኸታቸውን በየደረሱበት ሲያስተጋቡ የምንታዘባቸው ይሉኝታቢስ ወገኖች ዙሪያዋን በሌላ የቁጩ ከተማ ክርችም አድርጎ ማጠር ለምን እንዳስፈለጋቸው የሚያውቀው አንድዬ ብቻ ነው፡፡

__

በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena 
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,472FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

1 COMMENT

  1. Shegger = Addis Ababa = Addu Gennet = Berara

    We do not care what you name it or how wide you make it. This is your time in the sun and keep playing your shameful game. If you think you are strangling a people with your cruel, but childish, games, the rope you are using is going to be your hanging rope..

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here