
ቦርከና ዜና
በምርጫ ሰበብ ያለአግባብ የታፈኑ 7 የኮሌጃችን መምህራን እና 28 የተቋማችን ተማሪዎች በምስራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ የደህንነት ሰዎች በትናትናው ዕለት ከኮሌጁ ቅጽር ግቢ ተወስደዋል ሲል የደብረ ማርቆስ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አስታውቋል።
የትምህርት ተቋማት ለማንኛውም የፖለቲካ እንቅስቃሴ ማስፈፀሚያነት እንደማይውሉ እየታወቀ ባለፉት 30 ቀናት ውስጥ በኮሌጁ ግቢ ተማሪዎችን፣ መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞች በግዳጅ ከ5-7 የሚደርስ የምርጫ ካርድ በተለያዩ ስሞች እንዲያወጡ በመገደዳቸው ይህ ተግባር እንዲቆም ሲጠይቅ መቆየቱን አስታውሷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በቀን 29/2018 ዓ.ም የብልጽግና ፓርቲ በደብረ ማርቆስ ከተማ በጠራው የምርጫ ቅስቀሳ አልተሳተፋችሁም፤ የምርጫ ካርድም አላወጣችሁም፤ የተባሉ 7 የኮሌጃችን መምህራን እና 28 ተማሪዎቻችን በደህንነት ሰዎች ታፍነዋል ብሏል።
በቁጥጥር ስር የዋሉ መምህራን እና ተማሪዎቻችን እንዲለቀቁ ጠይቋል።
የደብረ ማርቆስ ከተማ ኮሚዩኒኬሽን በበኩሉ፣ የደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የፌስቡክ ገፅ ከሚያዚያ 27/2018ዓ.ም ጀምሮ ከተቋሙ ቁጥጥር ውጭ ሆኗል ብሏል።
የፌስቡክ ገጹ አድሚን የነበረው የተቋሙ ዲን አቶ አስጨንቅ ካሳ በጠላት ታፍነው በመወሰዳቸው ፔጁን ጠላት ሀሰተኛ መረጃ እያስተላለፈበት ይገኛል ብሏል።
የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ ፡ t.me/borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
ቦርከናን ለመደገፍ/ለማገዝ :- ይሄንን ይጫኑ
ፌስቡክ ገጻችንን ላይክ ያድርጉ ፡ Borkena
Ethiopian News–Borkena English






