By Admin on
ነፃ አስተያየት

-አዲስ ብር ገበያ ላይ ሲውል ሊፈታ ያልቻለው የዋጋ ግሽበትና ሌሎች የኢኮኖሚ ጉዳዮች- ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)ጥር 4, 2013 ዓ.ም. በወያኔ ዘመን ሲሰራበት የነበረውን የመገበያያ ገንዘብ በአዲስ እንዲተካ ሲደረግ የተሰራ መሠረታዊ ስህተት አለ። የዋጋ ግሽበት በከፍተኛ ጀረጃ እየናረ መምጣት የጀመረው የህወሃት አገዛዝ በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት በመመከርና በግፊት ከቋሚ የገንዘብ ልውውጥ(fixed exchange rate) ከዶላር ጋር ሲወዳደር ድሮ 2.05 […]
By Admin on
ነፃ አስተያየት

ይነጋል በላቸውጥር 4, 2013 ዓ.ም. “ካልደፈረሰ አይጠራም” እንዲሉ ነውና የሰሞኑ የችርቻሮ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ወቅቱን የጠበቀ እንደሆነ መግለጽ ወደድኩ፡፡ ከጥር ወር 2013 መባቻ ጀምሮ በአንድ ሊትር ቤንዚን ቀድሞ ከነበረው ዋጋ ላይ ሁለት ብር ገደማ ተጨምሯል፡፡ ግዴላችሁም ይሄ ጎደሎ ዓመት ብዙ ክስተት ሳያሳየን አይቀርም፡፡ (ሄኖክ አለማየሁ ይህችን ጽሑፍ ካየህልኝ ላንተ አንድ ወንድማዊ መልእክት አለኝ፤ የዩቲዩብ ዜናህን […]
By Admin on
ነፃ አስተያየት

ፈቃዱ በቀለ( ዶ/ር)ታህሳስ 13, 2013 ዓ ም በአገራችን ምድር ታዋቂ ግለሰቦችን ወይም የአንድ ድርጅት ሊቀ-መንበርን የማምለክ በሽታ አለ። በአስተዋፅዖቸው ሳይሆን በስም ብቻ ዝናን ያተረፉ ግለሰቦችን ማምለክ ተከታታይነትና ምሁራዊ መሰረት ለሚኖረው የድርጅት አወቃቀር እንቅፋት እየሆነ በምምጣት ላይ ነው። ከውስጥ ዲሞክራሲያዊና ፖሊሲ ነክ የሆኑ ነገሮች ላይ ክርክርም ኡኦነ ጥናት እንዳይካሄድ አመቺ ሁኔታዎችን ሲፈጥር አይገኝም። በፖለቲካ ድርጅት ስም […]
By Admin on
አበይት ዜና

ታህሳስ ፳፪ ቀን ፪ ሺህ ፲፫ ዓ.ም. ከሕግ መንግሥቱ ከመነጨው የፌዴራል ስርዓት የተነሳ የተጀመረው የዜጎች መፈናቀል እየከረረና እየመረረ መጥቶ ለዜጎች ሕይወትና ንብረት ውድመት ምክንያት ከሆነ ዓመታትን አስቆጠረ። ዛሬም እንደትናንቱ ዘርን መሠረት ያደረገው ጭፍጫፋ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በአንዳንድ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተጠናክሮ መቀጠሉን ስንሰማ የተሰማንን ሃዘን ለመግለጽ ቃላት ያጥረናል፡፡ በየትኛውም አገር ውስጥ በሥልጣን ላይ ያለ መንግሥት በዝቅተኛ […]
By Admin on
ነፃ አስተያየት

አያሌውታህሳስ 22 ቀን 2013 ዓ.ም. ጽሁፉን በፒዲኤፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
By Admin on
ነፃ አስተያየት

ከጥበበ ሳሙኤል ፈረንጅ፤ ታህሳስ 22 ቀን 2013 ዓ.ም “ ተስፋ መቁረጥ ቀላል ነው፤ ጣት መጠቆም ደግሞ የበለጠ ቀላል ነው” ዛክ ቴይለር። ከላይ የተጠቀምኩትን ጥቅስ የተናገሩት፤ የቀድሞው የሲንሰናቴ ባንግልስ የኳስ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት ዛክ ቴይለር ናቸው። አሰልጣኙ ይህንን የተናገሩት፤ እንደ አውሮፓ አቆጣጠር፤ በታህሳስ 1 2019፣ ቡድናቸው፤ የኒውዪርክ ጄት የተባለውን ቡድን በጠንካራ ፉክክር ካሸነፈ በኋላ ነው። ያሸነፍነው፤ […]
By Admin on
ነፃ አስተያየት

ተስፋዬ ደምመላሽታህሳስ 22 2013 ዓ. ም. አቅጣጫውን ጠብቆ የማያውቅና የታሰበለት ቦታ ደርሶ ዘላቂ ሰላም ሳያወርድ እንደወረርሽኝ በየጊዜው የሚያገረሸ የፖለቲካ “ለውጥ” አባዜ ኢትዮጵያን ከተጠናወታት ረጅም የአብዮትና የድህረ አብዮት ዘመን አልፏል። አንድ ትውልድ እያለፈ ሌላ እየተተካ ነው። ከጽንሱና ከአነሳሱ አገርን የለውጥ ባልቤት ከማድረግ ይልቅ የለውጥ ኢላማ ያደረገው ነባር የፖለቲካ ቅየራ እቅዶች ክትትል በተለይ ላለፉት ሦስት አስርተ አመታት […]
By Admin on
አበይት ዜና

ጋዜጣዊ መግለጫበፒዲ ኤ ፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ የብሔር ልዩነታችን ላይ መሰረት ባደረገ ፖለቲካዊ የአስተዳደር ስርዓት የዜጎችን መሰረታዊ ሰብዓዊ መብቶች ማረጋገጥ አይቻልም፡፡ በሀገራችን ኢትዮጵያ በንጹሃን ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለ አሰቃቂ ግድያ፣ የአካል መጉደል ፣ ለዘመናት ከኖሩበት ስፍራ መፈናቀል እንዲሁም ያፈሩትን ሃብትና ጥሪት በአንድ ጀንበር አጥተው ለተረጅነት መዳረግ በየጊዜው የሚያጋጥም የተለመደ አሳዛኝ ክስተት ሆኗል፡፡ ይህንን በዜጎች እየደረሰ […]
By Admin on
አበይት ዜና

መግለጫ በፒዲ ኤፍ ያንብቡት
By Admin on
ነፃ አስተያየት

አገሬ አዲስ ታህሳስ 17 ቀን 2013 ዓ.ም. የአንድ ቤተሰብ ሰላምና ክብር በሌሎቹ ዘንድ ሊጠበቅ የሚችለው የቤተሰቡ አባላት ፍቅራቸው የጠነከረ፣ ለክብራቸውና ለሰላማዊ ኑሮዋቸው ቀናዊ ሲሆኑ ነው።ሰላም፣ፍቅርና መተሳሰብ በሌለበት ቤተሰብ ውስጥ ሽኩቻ፣የእርስ በርስ ጠብና ግጭት መከሰቱ አይቀሬ ነው።ጠብና ግጭቱ በከረረ ቁጥር ቤት ይፈርሳል፣ቤተሰብም ይበተናል። በውጭ ይጠባበቅ የነበረው ደበኛ ወይም ዘራፊ ሰርጎ ለመግባትና ያሻውን ለማድረግ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርለታል። አድብቶ […]